TG Telegram Group Link
Channel: TIKVAH-ETHIOPIA
Back to Bottom
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል። ዛሬ ዓርብ ግንቦት 16 / 2016 በተጣለ ተተኳሽ ባል እና ሚስት ህይወታቸው አልፏል። አደጋው ያጋጠመው በትግራይ ክልል ፣ በማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ምረረ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በተተኳሹ ምክንያት የባል ህይወት ወድያው አልፏል። የሟች ሚስት ወደ…
#Tigray🚨

በሓውዜን ወረዳ በተጣለ ተተኳሽ #የ4_ሰዎች ህይወት ጠፋ።
 
በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች ፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል።

ሰኔ 1/2016 ዓ.ም በትግራይ ክልል በምሰራቃዊ ዞን ፤ ሓውዜን ወረዳ ማይጎቦ ቀበሌ ገበሬ ማህበር በፈነዳ ተተኳሽ የ4 ወገኖች ህይወት #ተቀጥፏል

ከአራቱ የአደጋው ሰለባዎች ሶስቱ የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሓውዜን ወረዳ ኮሙኒኬሽን ባገኘው መረጃ  ፥ ሟቾቹ ከ 9 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ገና ትንንሽ ልጆች ናቸው።

ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የሰኔ 1/2016 ዓ/ም አደጋን ጨምሮ በትግራይ የተለያዩ ወረዳዎች በተጣሉ እና በተቀበሩ  ተተኳሾችና ፈንጂዎች ከ107 ሰዎች ላይ የሞት ፣ የአካል መጉደል አደጋ ደርሷል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#ሴጅ_ማሰልጠኛ_ኢንስቲትዩት

ሰኔ 21 የሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የምስረታ ቀን ነው።

በማህበራዊ ገፆቻችን በሙሉ እየተከታተላችሁን ለዘለቃችሁ ቤተሰቦቻችን በሙሉ ምስጋናችን ከልብ ነው።

የምስረታ በዓላችንን ምክንያት በማድረግ ከሰኔ 01-21, 2016 ዓ.ም ድረስ ለምትመዘገቡ በሙሉ 20% ቅናሽ በሁሉም ትምህርቶቻችን ላይ ያደረግን መሆኑን ስንገልፅ በደስታ ነው።

Telegram: https://hottg.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute

ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻችን፦ ቁጥር 1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁጥር 2: መገናኛ
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ።

የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
#ጥቆማ

ከ3500 ዶላር እስከ 10 ሺ ዶላር የሚያሸልመው ለግብርና መሻሻል የሚረዱ የቴክኖሎጂ ውድድር መጀመሩን " አዩቲ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ሄፈር ኢንተርናሽናል የውድድሩ አዘጋጅ ባሳወቀው መሠረት፣ የውድድሩ ዓላማ የአርሶ አደሮች ምርታማነትን መጨመር የሚያስችሉ፣ ድካም የሚቀንሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ማቅረብ ነው።

ወድድሩ ሲካሄድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የሚወዳደሩት ከ18 - 30 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑና ተገልጿል።

የፈጠራ ሀሳባቸውን በ #ኦንላይን ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

የውድድሩ አሸናፊዎች በምን መልኩ ይለያሉ ?

➡️ ተወዳዳሪዎቹ ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ሀሳቦች 30ዎቹ በዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ ዳኞች በተገኙበት 30ዎቹ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ፣
➡️ ከ30ዎቹ 10 ሀሳቦችን ዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ 10ሩ ተወዳዳሪዎች ለ10 ቀናት ይሰለጥናሉ፣
➡️ ከስልጠናው በኋላ የመጨረሻ የ3 ተወዳዳሪዎች ሀሳብ ይመረጣል።

የሽልማት አሰጣጡ በምን መልኩ ነው ?

1ኛ ለወጣው 10 ሺህ ዶላር፣

2ኛ ለወጣው 6 ሺህ 500 ዶላር፣

3ኛ ለወጣው ሀሳብ ደግሞ 3 ሺህ 500 ዶላር የሥራ ማስጀመሪያ እና የማበረታቻ ሽልማት ይደረግላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በተካሄዱት 2 ውድድሮች የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮሩ አጠቃላይ 12 የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ መዋላቸው ተነግሯል።

ማመልከቻ ፦ https://ayute-ethiopia.et/apply-here/

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@TikvahEthiopia
#CPPI #WorldBank

የዓለም ባንክ ከኤስ ኤንድ ፒ ግሎባል ማርኬት ኢንተለጀንስ ጋር የሚያዘጋጀው የኮንቴይነር ወደብ የአፈጻጸም መለኪያ (Container Port Performance Index - CPPI) የ2023 ደረጃ ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል።

ይህ መለኪያ ወደቦች የመረከብ አቀባበላቸውንና እንዴት እንደሚያስተናግዱ በአጠቃላይ ያላቸውን የስራ ቅልጥፍና እና አፈጻጸም የሚለካ ነው።

በዚህም ከ409 ወደቦች የራስ ገዟ #ሶማሌላንድ " #በርበራ " ወደብ 106ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የሶማሊያ ፤ " #ሞቃዲሾ " ወደብ ደግሞ 166ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የ " #ጅቡቲ " ወደብ ከመጨረሻ ተርታ 379ኛ ደረጃ ላይ ነው የተቀመጠው።

በዚህ የዓለም ባንክ የአፈጻጸም መለኪያ የበርበራ ወደብ ከሞቃዲሾ እና ጅቡቲ ወደቦች የተሻለ ደረጃ ተሰጥቶታል።

በአጠቃላይ ዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሰጣቸው ከ405 ወደቦች በመጨረሻ ተርታ ማለትም 379 ላይ የተቀመጠው የጅቡቲ ወደብ በሀገሪቱ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል።

የጅቡቲ ወደብ በ2022 ከዓለም የተሰጠው ደረጃ 26ኛ ሲሆን በ2023 መለኪያ 379ኛ ላይ መቀመጡ ጅቡቲን አላስደሰተም።

ሀገሪቱ " የ2023 ደረጃ አሰጣጥ ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ ያሳስበናል " ያለች ሲሆን " ምን አይነት ሳይንስ ነው የሚያብራራው በዓለም ደረጃ ከ350 በላይ ነጥብ መጣል ? " ስትል ጠይቃለች።

በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለው ደረጃ መሰጠቱ በመለኪያው ላይ የተዓማኒነት ጥያቄ እንደሚያስነሳ ገልጻለች።

ጅቡቲ ፥ " ደረጃ አሰጣጡ ነጻ እና ከተእጽኖ የጸዳ ነው ወይ ? " ስትል ጠይቃ " ለማንኛውም አድሏዊም ሆነ አልሆነ ጅቡቲ ከሰሃራ በታች እና ምስራቅ አፍሪካ ትልቁ እና ቀልጣፋ ማዕከል ናት " ብላለች።

ሙሉ ዶክመንቱን በዚህ ያግኙ ➡️ CPPI 2023

#WorldBank

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
የሕብረት ባንክ ማህበራዊ ገፆቻችንን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ቴሌግራም: https://hottg.com/HibretBanket
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/HibretBank
ሊንክዲን: https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/hibretbank/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@hibretbanket

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
#ሪልስቴት #አዲስአበባ

° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች

° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ የገቡበት ቤት፦
- ውሃ፣
- መብራት፣
- ጀነሬተር
- የውሃ ታንከር የሚባሉ መሠረት ልማቶች እንደሌሉ ገልጸዋል።

ቤት ገዢዎቹ ከዚህ ቀደም፣ “ ቅሬታ ባቀረብንበት ወቅት የኖህ ጠበቃ በ1 ወር ከ 15 ቀን ጊዜ ውስጥ የጋራ መሠረተ ልማቶች አጠናቀው እንደሚያስረክቡ ቃል ተገብቶልን ነበር ” ሲሉ አስታውቀዋል።

“ እስካሁን እንኳን ሊጨርሱ ምንም እንቅስቃሴ የለም ” ብለው፣ “ ቤት ውስጥ የገቡ ቤት ገዢዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል። መብራት የለም፣ ውሃ የለም፣ ውሃ ታንከር የለም ” በማለት አማረዋል።

“ እነዚህ መሰረተ ልማቶችን ውላችን ላይ አሟልተው እንደሚሰጡን ተስማምተን ነው ቤቱን የገዛነው። ኖህ ውሉን ጥሷል ” ነው ያሉት።

“ ይባስ ብሎ ቤት ገዢ #የቤት_ክራይ_ሽሽት ወደገዛው ቤቱ መሰረታዊ ነገር ባልተሟላበት ሁኔታ ለመግባት ተገዶ መብራት በሳይቱ ዙርያ ካሉ ቤቶች በህገወጥ መንገድ ለመቀጠል ተገዷል ” ሲሉ አክለዋል።

“ ግቢው በተጠላለፈ የኤሌትሪክ ገመድ በገመድ ሆኗል ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ “ ይህ ለሚኖሩት ሰዎችም ሆነ ለልጆቻቸው ትልቅ አደጋ ይፈጥራል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ሁነቱን የሚያሳይ ቪዲዮም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ልከዋል።

በጠበቃቸው በኩል ኖህ ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ምላሽ እንዳልሰጣቸው አስረድተው " የመፍትሄ ያለህ " ብለዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት ጠበቃቸው ለኖህ ሪልስቴት የጻፈው ደብዳቤ ፥ ኖህ የቤቶቹን መሠረተ ልማት እያሟላ እንዳልሆነ፣ ምላሽ እንዲሰጥ ቢጠይቅም ምላሽ እንዳልሰጠ ያትታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ላነሷቸው እያንዳንዱ የቅሬታ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ ኖህ ሪልስቴትን ጠይቋል።

የድርጅቱ የሕግ አማካሪ እና ጠበቃ አቶ ዮሴፍ ደስታ በሰጡት ቃል፣ “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” ብለዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-10

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

" መኪና አቁሞ መሄድ ፍጹም የተከለከለ ነው " - ፖሊስ

የኮሪደር ልማት ስራዎቻቸው ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት በተደረጉት መንገዶች ላይ ተሸከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ ክልክል መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከ5ቱ የኮሪደር ልማት ስራዎች ውስጥ ፦

➡️ ከአራት ኪሎ እስከ ቅ/ማሪያም ቤ/ክርስቲያን መታጠፊያ
➡️ ከቴዎድሮስ አደባባይ እስከ መሐሙድ ሙዚቃ ቤት እንዲሁም
➡️ ከቀይ ባህር ኮንዶሚኒየም በደጎል አደባባይ እስከ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን አቅጣጫ መንገዱ ትላንት ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ ለአገልግሎት ክፍት በተደረጉት መንገዶች ላይ ተሸከርካሪዎችን አቁሞ መሔድ ፍጹም ክልክል መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#Malawi

ዛሬ የማላዊውን ምክትል ፕሬዝዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች 9 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተሰውሯል።

እንደ አገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አውሮፕላኑ የማላዊ መከላከያ ኃይል ንብረት ነው።

ጥዋት ከሀገሪቱ ዋናው ከተማ ሊሎንዌ ከተነሳ በኋላ " ከራዳር ዕይታ ውጪ " ሆኗል። ምን ውስጥ ይግባ አይታወቅም።

የአገሪቱ የአቪዬሽን ባለሥልጣናት ከአውሮፕላኑ ጋር ግንኙነት ለማድረግ ሞክረው ነበር ግን አልቻሉም።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንትም #የፍለጋ እና #ነፍስ_የማዳን ተልዕኮ እንዲካሄድ አዘዋል።

ም/ ፕሬዝዳንቱ መንግሥትን ወክለው በአንድ የቀድሞ የም/ቤት አባል የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ነበር በረራ የጀመሩት።

አብረዋቸው በርካታ የፓርቲያቸው ባለሥልጣናት ነበሩ።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Malawi ዛሬ የማላዊውን ምክትል ፕሬዝዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች 9 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተሰውሯል። እንደ አገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አውሮፕላኑ የማላዊ መከላከያ ኃይል ንብረት ነው። ጥዋት ከሀገሪቱ ዋናው ከተማ ሊሎንዌ ከተነሳ በኋላ " ከራዳር ዕይታ ውጪ " ሆኗል። ምን ውስጥ ይግባ አይታወቅም። የአገሪቱ የአቪዬሽን ባለሥልጣናት ከአውሮፕላኑ ጋር ግንኙነት ለማድረግ…
#Malawi

የማላዊ ምክትል ፕሬዜዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች ባለስልጣናትን ይዞ ከራዳር እይታ ውጭ የሆነውን እና የገባበት ያልታወቀውን አውሮፕላን ፍለጋ እየተካሄደ ነው።

ፍለጋው እየተካሄደ ያለው በመከላከያ ወታደሮች ፣  በፖሊስ አባላት እንዲሁም በሌሎች ሲቪል ዜጎች እንደሆነ ተነግሯል።

የሀገሪቱ መንግስት #ያሰማራው_ኃይል እንዲህ አይነቱን ፍለጋ ለማድረግ አቅም ስለሌለው እና ምንም ማድረግ ስለማይችል ልክ እንደ ማንኛውም ሲቪል እየተንቀሳቀሰ ነው እየፈለገ ያለው።

ምናልባትም " አውሮፕላኑ ወድቆ ይሆናል " ተብሎ በታሰበበት ጫካ ውስጥ ፍለጋ በእግር እና በመኪና እየተካሄደ እንደሚገኝ ነው የተሰማው።

በርካታ የሀገሪቱ ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ም/ፕሬዜዳንቱ እና አብረዋቸው ያሉት ሰዎች " ጥሩ ነገር አልገጠማቸውም " የሚል ስጋታቸውን እያጋሩ ነው።

ም/ፕሬዜዳንቱ አብረዋቸው በርካታ የፓርቲያቸው ባለሥልጣናት ነበሩ።

የሀገሪቱ መንግሥት ለእንደዚህ አይነት አደጋ ወቅት የሚሆን ዝግጁነትና ለፍለጋ የሚሆኑ መሳሪያዎችን እንኳን አላሟልም በሚል እየተተቸ ነው።

አውሮፕላኑም ከተሰወረ ከረጅም ሰዓታት በኃላ ነው ለህዝቡ ያሳወቀው።

በቅርቡ ፥ የኢራን ፕሬዝዳንት የነበሩት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለስልጣናት በስራ ጉዳይ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር ጫካ ውስጥ ተከስክሶ ሁሉም መሞታቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Malawi የማላዊ ምክትል ፕሬዜዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች ባለስልጣናትን ይዞ ከራዳር እይታ ውጭ የሆነውን እና የገባበት ያልታወቀውን አውሮፕላን ፍለጋ እየተካሄደ ነው። ፍለጋው እየተካሄደ ያለው በመከላከያ ወታደሮች ፣  በፖሊስ አባላት እንዲሁም በሌሎች ሲቪል ዜጎች እንደሆነ ተነግሯል። የሀገሪቱ መንግስት #ያሰማራው_ኃይል እንዲህ አይነቱን ፍለጋ ለማድረግ አቅም ስለሌለው እና ምንም ማድረግ ስለማይችል…
" ፓይለቱ ወደ ኃላ እንዲመለስ ተነግሮት ነበር ፤ ከዛ በኃላ ግን አውሮፕላኑ የት እንደገባ አልታወቀም " - የማላዊ ፕሬዜዳንት

የተሰወረው የማላዊ አውሮፕላን አልተገኘም።

በአውሮፕላኑ ውስጥ ከም/ፕሬዜዳንቱ ጋር የቀድሞው ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ ባለቤት / የቀድሞ ቀዳማዊ እመቤት ሻኒል ዲዚምቢሪ እንደሚገኙበት ተነግሯል።

አንዳንድ ሚዲያዎች እና የቀድሞ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ " በጣም ድቅድቅ ጨለማ ሆኗል " በሚል " በቃ ነገ ጥዋት ይቀጥላል ተብሎ " ፍለጋው እንደቆመ ተናግረዋል።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ላዛሩስ ቻክዌራ ለሊቱን በሰጡት መግለጫ " ይሄ ውሸት ነው ምንም የቆመ ፍለጋ የለም ፤ የመከላከያ ወታደሮች በስፍራው ላይ ፍለጋ ላይ ናቸው " ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ ፕሬዝዳንቱ ለፍለጋው ጎረቤት ሀገራትን እና የአጋር ሀገራት አሜሪካ ፣ ኖርዌይ ፣ እስራኤል ፣ ዩናይትድ ኪንግደም መንግሥታትን " አፏልጉኝ " ሲሉ እገዛ እንደጠየቁ አሳውቀዋል።

ፕሬዜዳንቱ አውሮፕላኑ ከዋና ከተማ ሊሎንግዌ ተነስቶ ወደ መዳረሻው መዙዙ ከተማ ሲጓዝ እንደነበር ገልጸዋል።

ነገር ግን ፓይለቱ በመጥፎ የአየር ሁኔታ የተነሳ ለእይታ ምቹ ሁኔታ ስላልነበር አውሮፕላኑን ማሳፈር እንዳልቻለ ፤ በኃላም የአቪዬሽን ሰዎች ወደ ኃላ (ሊሎንግዌ) እንዲመለስ እንደተነገሩት ከዛ በኃላ ግን የት እንደገባ እንዳልታወቀ አስረድተዋል።

አውሮፕላኑ ምክትል ፕሬዜዳንቱን ጨምሮ በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ይዞ ነበር።

#Malawi #ChilimaMissingPlane

@tikvahethiopia
HTML Embed Code:
2024/06/11 02:54:20
Back to Top