#ወደ_ሮሜ_ሰዎች
ክፍል 55 መ
የኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን የማንጻት ሥራ ግን የመማለድ የማማለድ ሀሳብ የለውም።
ልማልድ ወይም ልለምን ራሱ ቢል አብ የሚባለው የባህርይ አባቱ እና ከእርሱ ጋር በዕሪና ያለ እና የሚተካከል ነው።
- ዕብራውያን 7:25
ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።
...ሊያማልድ ዘወትር በህይወት ይኖራል ማለቱ ስለ ፍጹም የማዳን ፍቅሩ ስለ ርህራሄው የተገለጸ ነው ምክንያቱም ከታች
በጌታ አምነው ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ያድናቸዋል የሚል አሳብ ተናግሯል።
በእውነት ጌታ እንደ ጥሬ ቃሉ አማላጅ ቢሆን ማዳን አይችልም ነበር።
ሌላኛው ጌታ እነዚህ የምልጃ እና የልመና ቃላት ቢነሱበት ስለ ነገረ ሥጋዌ(ስለ ሰውነቱ)የተነገሩ ናቸው።
መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ ሰው በመሆኑ አይደለም ከአብ ከመላእክት አንሶ መቆጠሩን ይነግረናል።
Hebrews 2 አማ - ዕብራውያን
9: ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ ስለ ሰው ሁሉ ሞትን ይቀምስ ዘንድ፥ ከመላእክት ይልቅ በጥቂት አንሶ የነበረውን ኢየሱስን ከሞት መከራ የተነሣ የክብርና የምስጋናን ዘውድ ተጭኖ እናየዋለን።
በሌላ በኩል መጽሐፍ ቅዱስ በባህርይው አንዳንድ ጊዜ የተፈጸመን ነገር ወደ ፊት እንደ ሚፈጸም አድርጎ ይናገራል።
ለዚህም ጌታ በመስቀል ላይ በዕለተ አርብ
ስለ ሰው ልጆች ስለ ቀደመው አዳም
ዳግማዊው አዳም ክርስቶስ በእርሱ ቦታ ተገብቶ የሰው ልጆችን ጩኸት የጮኸበትን ያንን ሀሳብ ሐዋርያው
ገና ወደ ፊት እንደ ሚፈጸም አድርጎ ያቀርበዋል።
ሉቃስ 23 34: ኢየሱስም፦ “አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው፡” አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት።
ስናጠቃልል ለጌታ ከላይ እስካሁን ያየናቸው የምልጃ ቃላት ተነግረዋል።
ሲጠቃለል:-ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አማላጅ አይደለም።
ነገር ግን የምልጃ የልመና ቃላቶች ለእርሱ ተነግረዋል ይህም ስለ ፍጹም ፍቅሩ ርኅራሄው፣ስለ ደሙ ፍጹም የማንጻት ሥራ እና ስለ ሌሎችም ነገሮች
ይቀጥላል ......
@eotchntc
>>Click here to continue<<