TG Telegram Group Link
Channel: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Back to Bottom
Forwarded from ተውሒድ የሁሉም ነብያቶች ጥሪ ነው። (Bint Mohammed አላህ ከዐርሹ በላይ ነው።)
አሠላምአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ

ውድና የተከበራችሁ እህት ወንድሞች ይች እህታችን ስሟ ተምሬ አራጋው ጎቸል ትባላለች ከፓስፖርቱላይ እንዳለው በጠለብ ከአራትና አምስት ወር በፊት ሳኡድ ጂዳ ከተማ ገብታ ነበር እናም አሰሪዋ መንገድ ላይ ጥላታለች አሉን። አእምሮዋም ትክክል አይደለም ቪዶወውላይ እንደምታዩት።የቀረጿትም ልጆች ልንወስዳት ስንል ሴትየዋ እምቢአለችን አሉ በሰአቱ ዘወር ብለው ሲመለሱም ከቦታው እንዳላገኙዋት ነው የተናገሩት እና ጂዳ አካባቢ ያላችሁ በተለይ እባካችሁ ይችን እህታችንን ያያት ካለ እንድትተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን።

አላህ ሁላችንም ይጠብቀን እሷንም ያስገኛት!!

እኔ የሰፈሯ ልጂ ነኝ ካገኛችኋት

0532053175 Bint Mohammed በዚህ ቁጥር በዋሳብም ወይም በመስመር ያገገኙኛል ይደውሉ የሠማችሁም አደራ ሸር አድርጉልኝ
የኪታብ ጥቆማ #20
~
* የኪታቡ ስም:— شرح العقيدة التدمرية
* አዘጋጁ:– ዐብዱረሕማን ብኑ ናሲር አልበራክ
* ኪታቡ ተድሙሪያን ድንቅ በሆነ መልኩ የተነተነ ነው። ገዝታችሁ በጥልቀት አንብቡት። ትጠቀሙበታላችሁ።
* ሶፍት ኮፒ የሚፈልግ በዚህ ሊንክ ማግኘት ይችላል:-
https://hottg.com/c/1269314107/262656
=
https://hottg.com/IbnuMunewor
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በሱፊያው ዓለም በርካታ የሚመለኩ ቀብሮች አሉ። ቀብሮቹ ዘንድ በመሄድ ልጅ፣ ዝናብ እና የተለያዩ ሐጃዎችን ይማፀናሉ። የሞተ ሰው እንኳን የነሱን ጉዳይ ሊፈፅም ከራሱ፣ ከተሰራለት ዶሪሕ እንኳ መከላከል አይችልም። ይሄው ይሄ "ወሃቢ" የሆነ ጎርፍ ዶሪሑን ነቅሎ እየወሰደው ነው።
{ أَیُشۡرِكُونَ مَا لَا یَخۡلُقُ شَیۡـࣰٔا وَهُمۡ یُخۡلَقُونَ (191) وَلَا یَسۡتَطِیعُونَ لَهُمۡ نَصۡرࣰا وَلَاۤ أَنفُسَهُمۡ یَنصُرُونَ (192) }
"ምንንም የማይፈጥሩትንና እነርሱም የሚፈጠሩትን (በአላህ) ያጋራሉን? ለእነርሱም መርዳትን የማይችሉትን ነፍሶቻቸውንም የማይረዱትን (ያጋራሉን)?" [አልአዕራፍ፡ 191-192]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
መስጂድ'ኮ አይመለክም
~
ለጭንቅ ለችግራችሁ የምትጠሩት ዶሪሕ እንኳን ለናንተ ሊደርስ ራሱንም ጎርፍ ወሰደው ስል "ከሰሞኑ ሳውዲ ላይ አንድ ትልቅ መስጊድ በዝናብ ምክንያት ተደርምሷል አንተ እንደምትለው ከሆነ እሱም የሱፍዮች ይሆን እንዴ?" ይለኛል።
እኛ በእምነታችን መስጂድ ለጭንቅ ለችግር ይደርሳል ብለን የምናመልክ አይደለንም'ኮ ያ ሱፊ! እናንተ መስጂድ ታመልካላችሁ እንዴ? "አቅም አለው፤ አገር አቆራርጦ የተቸገረን ይረዳል፤ በቀብሩ ዙሪያ የሚሰበሰቡ ተማፃኞችን ጩኸት ይሰማል ይረዳል፣ ..." እያልክ የምታመልከው ሙታን ቀብር ላንተ ሊደርስ ቀርቶ ራሱንም ማዳን አልቻለም ስትባል "ሳውዲ ላይ አንድ ትልቅ መስጊድ በዝናብ ምክንያት ተደርምሷል" ትላለህ? ሳዑዲ ውስጥ መስጂድ ይመለካል ብለህ ነው እንዴ የምታስበው? ሳዑዲ ውስጥ የስንት አኢማ ቀብር አለ። ግን አይመለክም። የነብዩ ﷺ ቀብር አለ። ግን አይመለክም። እንዲያውም ፖሊስ አቁመው፣ አስተማሪ መድበው ነው የሚከላከሉት።

ደግሞ እወቅ! እንኳን ሌላ መስጂድ ከዕባም በጎርፍ ተጠቅቶ እንደገና የተሰራበት ጊዜ አለ'ኮ። የከዕባ መጋረጃ የተቃጠለበት ጊዜ አለ። ከዕባ ለጭንቅ ለችግር ሊደርስ ቀርቶ ራሱን ማዳን ይችላል ብለንም አናምንም። ባጭሩ እኛ ከዕባን አናመልክም።
እንዲያውም የተከበረው ሐጀረል አስወድንም አናመልክም። ይህንን ድንቅ ታሪክ ተመልከት። ታላቁ ሶሐቢይ ዑመር ብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) በመቅረብ ከሳሙት በኋላ እንዲህ አሉ:-
إِنِّي أَعْلَمُ أَنَّكَ حَجَرٌ لَا تَضُرُّ وَلَا تَنْفَعُ، وَلَوْلَا أَنِّي رَأَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يُقَبِّلُكَ مَا قَبَّلْتُكَ.
“እኔ አንተን የማትጎዳ የማትጠቅም ድንጋይ እንደሆንክ አውቃለሁ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሲስሙህ ባላይ ኖሮ ባልሳምኩህ ነበር፡፡” [ቡኻሪ፡ 1597] [ሙስሊም፡ 1270]

ቁልፉ ነገር ሙታን አታምልኩ ነው። "አናመልክም" እያሉ መዋሸት ራስን ማታለል ነው። በደንብ ነው ሙታን የምታመልኩት። ለጭንቅ ለችግር ሙታንን መማፀን አምልኮት አይደለም? የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦
"الدُّعَاءُ هُوَ الْعِبَادَةُ، قَالَ رَبُّكُمُ : {ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}"
"ተማፅኖ አምልኮት ነው። ጌታችሁ፡ {ለምኑኝ፤ እቀበላችኋለሁና} ብሏል።" [አቡ ዳውድ፡ 1479]

ከዚህም አልፈው መቃብር ዘንድ በመሄድ ስለት የሚፈፅሙ፣ እርድ የሚያርዱ፣ ሱጁድ የሚወርዱ፣ ... ብዙ ናቸው። ስለዚህ "ሙታን አናመልክም" እያሉ በገሃድ የሚታየውን ነገር መሸምጥጥ ራስን መሸወድ ነው። የመካ ሙሽ ሪኮች እንኳ ማመሀኛ ይደረድራሉ እንጂ ማምለካቸውን አልካዱም። ቁርኣን ምስክሬ ነው።
1. {وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ}
"እነዚያም ከርሱ ሌላ ረዳቶችን የያዙት 'ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቀርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቸውም' (ይላሉ።)" [አዙመር፡ 3]
2. {وَيَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمۡ وَلَا يَنفَعُهُمۡ وَيَقُولُونَ هَٰٓؤُلَآءِ شُفَعَٰٓؤُنَا عِندَ ٱللَّهِۚ}
"ከአላህም ሌላ የማይጎዳቸውን እና የማይጠቅማቸውን ያመልካሉ። 'እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው' ይላሉም።" [ዩኑስ፡ 18]

ይሄ የአጋሪዎቹ ማመሀኛ ዛሬም የሙታን አምላኪዎች ማመሀኛ ነው። እንጂ ጣኦቶቻቸው ከአላህ በታች እንደሆኑ ያምኑ ነበር። ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ እንዲህ ይላሉ፡-
كَانَ الْمُشْرِكُونَ يَقُولُونَ: لَبَّيْكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، قَالَ: فَيَقُولُ رَسُولُ اللهِ ﷺ: «وَيْلَكُمْ، قَدْ قَدْ» فَيَقُولُونَ: إِلَّا شَرِيكًا هُوَ لَكَ، تَمْلِكُهُ وَمَا مَلَكَ، يَقُولُونَ هَذَا وَهُمْ يَطُوفُونَ بِالْبَيْتِ
“አጋሪዎቹ 'አቤት ለአንተ ተጋሪ የለህም' ይሉ ነበር። ይህን ሲሉ የአላህ መልእክተኛ ﷺ 'ወዮላችሁ በቃ በቃ!' ይሏቸው ነበር። እነሱ ግን 'የምትቆጣጠረው የማይቆጣጠርህ ላንተ የሆነ ተጋሪ ቢሆን እንጂ' ይላሉ። ይህን የሚሉት ከዕባን እየዞሩ (ጠዋፍ ሲያደርጉ) ነው።” [ሙስሊም፡ 1185]

በሱፊያ ማደንዘዣ የተሸወድክ ወገኔ ሆይ! ንቃ!

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
Live stream finished (1 hour)
Riyadh #153
Ibnu Munewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣5️⃣3️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://hottg.com/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 462፣ ሐዲሥ ቁ. 1324
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
「𑁍📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ 𑁍」

╭┄┈┈
│ሱነኑ አቢ ዳውድ سنن أبي داود

🎙የደርሱ አቅራቢ »
│⚊⚊
│» ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
╰─────────────────╯
🏷በ5 አፕሊኬሽን ተዘጋጅቶ የቀረበ
╭𑁍──────────────
│➺ቁጥር 1 ከሐዲስ 01-1268
🖇 https://hottg.com/Yusuf_App1/509
├𑁍──────────────
│➺ቁጥር 2 ከሐዲስ 1269-2184
🖇 https://hottg.com/Yusuf_App1/510
├𑁍──────────────
│➺ቁጥር 3 ከሐዲስ 2185-3203
🖇 https://hottg.com/Yusuf_App1/511
├𑁍──────────────
│➺ቁጥር 4 ከሐዲስ 3204-4354
🖇 https://hottg.com/Yusuf_App1/512
├𑁍──────────────
│➺ቁጥር 5 ከሐዲስ 4355-መጨረሻው
🖇 https://hottg.com/Yusuf_App1/513
╰𑁍──────────────
⎙ አሁኑኑ ዳውንሎድ በማድረግ ይጠቀሙ!
↻ ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
⎘ ለመሰል ስራዎች ይቀላቀሉን
𑁍
http://hottg.com/Yusuf_App1
ኢብኑ ቁዳማ አልመቅዲሲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
"አብዛኞቹ ሰዎች የጠፉት የሰዎችን ውግዘት በመፍራት እና ሙገሳቸውን በመሻት ነው። በዚህ የተነሳ እንቅስቃሴያቸው እንዳለ ሰዎችን ከማስደሰት ጋር በሚገጥም መልኩ ይሆናል። ይህም ሙገሳን በመሻትና ውግዘትን በመፍራት ነው። ይሄ አጥፊ ስለሆነ ሊታከም ግድ ይላል።"
"ሙኽተሶሩ መንሃጂል ቃሲዲን፡ 212]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የቴሌግራም ቻናል፡- https://hottg.com/IbnuMunewor
ጭፍራው ቅርቃር ውስጥ ገብቷል
~
ቅልጥ እንደ ቅቤ - ፍርስ እንደ ሸክላ
ሁሉ ነገር እርቃን - እነ ሳይሞቅ ፈላ!

ይሄ ሰካራም ጭፍራ ብዙ እንደማይራመድ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ። በዚህ ፍጥነት ድንብርብሩ ሲወጣ፣ ጉዱ ሲዝረከረክ ማየት ግን የጠበቅኩት አልነበረም። የዛሬን ሁለት ዓመት መሰለኝ ወራቤ ላይ አንድ ወንድም ዐብዱልሐሚድ ለተሞ አንድ መንሀጅ ላይ ሁለት አመት ታግሶ መቆየት አይችልም ጠብቁ ሲል ሰምቼው ነበር። ምናልባት የሆነ ያክል ተጋኖ ይሆን? አላውቅም። ንግግሩ ግን በውስጡ የሆነ እውነት አዝሏል። አሁን ላይ አንዳንድ ነገሮች ጫፋቸው እየዘለቀ ነው። እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል እንዲሉ ይሄው እየጠራ መጣ። በየጊዜው እየወጡ ካሉ በርካታ የቪዲዮ እና የፎቶ ማስረጃዎች ውስጥ ለጊዜው አንድ ማሳያ ልጥቀስ፦

ጠሃ ኸዲር የዚህ የተንቀዠቀዠ ጭፍራ አጫፋሪ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ሶሻል ሚዲያ ላይ እየዘለቀ ሁለት ሶስት መስመር ስድብ መፃፍን ቁም ነገር ያደረገ በተግባር ግን በተለያየ ቦታ የተለያየ ፊት የሚጠቀም ሰው ነው።
* ሳዑዲ ውስጥ ጤነኛ ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ቁጭ ብሎ ለአመታት ይማራል። እዚህ ደግሞ እነ እከሌ ከእነ እከሌ ጋር ተቀመጡ እያለ ፎቶ ይለጥፋል። የሳዑዲ ኤምባሲ ሲጋብዛቸው ራሱም ጭፍራዎቹም ከነዚያው ከሚያወግዛቸው አካላት ጋር አንድ ላይ ይጣዳሉ። በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ፊት ማሳየትን ተክኖበታል።
* መሻይኾች ዘንድ ሌላ ሰው ነው። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ደግሞ ሌላ።
* ሳዑዲ ውስጥ ሌላ ሰው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ።
* እንደ ባህሩና ሑሴን ያሉ ተናካሽ ጓዶቹ ጋር ሲሆን ሌላ ነው። አቃቂር እያወጡ፣ ቅጥፈት እየለጠፉ የሚናከሱ አውሬዎች ናቸው። እያደናነቀ የሚያስተዋውቃቸው የሀረር አካባቢ ጭፍራዎቹ ደግሞ እሱ በሚስላቸው 'ሙስተዋ' ላይ አይደሉም። ያያያዝኩት ቪዲዮ ለዚህ አንድ ምስክር ነው።
በቪዲዮው ላይ የጠሀ ጭፍራ የሆኑት (የነበሩት ብለው ይሻል ይሆን?) እነ ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ (ጭሮ?) ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር ተቀማምጠው የአንድነት መግለጫ ያወጡበት ጉባዔ ነው። ቪዲዮው ላይ ከሰፈረው ቃል ቀንጨብ ላድርግ፦

1- የዶክተር ጀይላን ንግግር፦

"የሀረር ዑለማኦች ህብረት እና የኦሮሚያ ዑለማኦች ህብረት ከኢትዮጵያ ዑለማኦች ህብረት ጋር አንድ ሆነው ሲወያዩ ውለዋል። በፊርቃ ስም የሚሰጣጡ፣ ወደዛ ወደዚህ እያሉ አንዱ ባንዱ ላይ የሚፅፉ፣ በዑለማእ ስም የሚነግዱ ስላሉ፤ ሸይኾች ሸይኽ ኢልያስ ዐባስና ሸይኽ አሕመድ ከዑለማኦች ጋር አንድ ሆነዋል። ከአህለ ሱና ወልጀማዐ ዑለማኦች ጋር፣ ከመጅሊስ ዑለማኦች ጋር እጅና ጓንት ሆነን አንድ ላይ ሆነን እንሰራለን ብለው (ቃል) ገብተውልናል።
በስማቸው ከሚነግዱባቸው ሰዎች ራሳቸውን ነፃ ያድርጉ።"

ከዚያ እነ ጠሀ በስማቸው የሚነግዱባቸው ሁለቱ ሰዎች ራሳቸውን ነፃ አድርገው ተናገሩ። ይሄውና፡

2- የኢልያስ ዐባስ ንግግር፦

"እኛ ዓሊሞቻችን ሸይኾቻችን ሸይኽ ሙሳ እና ዶክተር ጀይላን እንዲሁም ሌሎችም አሉ። ድሮም የተጣላነው ነገር የለም። አብረን ነበር። አሁንም አብረን ነን። ከዚህም በኋላ አብረን ነን፣ እስከ ዘላለም። ዓሊሞችን ከሚሳደብ የጠራን ነን።"

3- የአሕመድ ሙሐመድ ንግግር:-

"እኛ ከታላላቅ ሸይኾቻችን ጋር ነን። ድሮም ከነሱ ጋር ነበርን። አሁንም ከነሱ ጋር ነን። እነሱን ከሚሳደብ ሰው ድሮም አሁንም ንፁህ ነን።"

ልብ በሉ! ጠሀ ኸዲር እነዚህን ሁለቱን ሰዎች (ማለትም ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ) ሞቅ አድርጎ ያወድሳል። ያሰራጭላቸዋልም፡፡ ለምሳሌ ያክል በቅርቡ እንዲህ ሲል ፅፏል:-

"أشد على أيديكم يا أبطال شرق هرر فضيلة الشيخ Sheek Iliyaas Abbaas
وفضيلة الشيخ Shekh Ahmade Muhammed
زادكم الله قوة إلى قوتكم
فقد أقضت جهودكم المضاجع وألهبت المشاعر وأسهرت وهزت ولن يهنأ منهم أحد مهما كان بعدما التهبت الأحشاء واضطرمت!"

እነዚህ የጠሀ ጀግኖች ግን፡

1ኛ፦ ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር፣ እንዲሁም በጠቅላላ ከመጅሊስ ሰዎች ጋር አንድ እንደሆኑ ድሮም፣ አሁንም በመካከላቸው ልዩነት እንደሌለ ገልፀዋል። እስከ ዘላለም ከነሱ እንደማይለዩም አስረግጠው ተናግረዋል።
2ኛ:- እነሱን (እነ ዶክተር ጀይላንን) ከሚሳደቡ አካላት ድሮም አሁንም ንፁህ ነን። ፈፅሞ እነሱን ከሚሳደቡ ጋር አንሆንም ማለታቸውን ያዙ። እዚህ ላይ ቁጥር አንድ ተጠቃሹ ጠሀ ኸዲር ነው። አሞሌው አልሰራም።

ከዚህ በኋላ ያለው ምርጫ ሁለት ነው።

1ኛው ምርጫ፦ ወይ እንደ ግለቱ እያዩ ሲያሻቸው "እኛ ድሮም ጀምሮ መንሀጅ ገብቶናል፣ ለ20፣ ለ30 አመታት ሰለፊያን (የነሱን ቨርዥን) ስናስተምር ነው የኖርነው፣ ከኢኽዋን የጠራን ነን፣ ..." እያሉ መሞገት፤ ሲላቸው ደግሞ ከነዚያው ኢኽዋን ከሚሏቸው ሰዎች "ድሮም አሁንም አንድ ነን፣ ዘላለም አንለያይም" እያሉ የጋራ መግለጫ እያወጡ መቀጠል ነው። በተለያየ መመዘኛ እየመዘኑ፣ የተለያየ ፊት እያሳዩ መሄድ ለጠሀ ከባድ አይመስለኝም። ይሄ ግን የሰለፊ መገለጫ አይደለም። ሸይኽ ሙቅቢል እንዲህ ይላሉ፦
فالحزبي مستعد أن يكون له خمسة أوجه. والنبي ﷺ يقول: إن من شر الناس ذا الوجهين الذي يأتي هـولاء بوجه وهؤلاء بوجه.
أما السني فإنه متمسك بدينه سواء رضي فلان أو لم يرضَ بخلاف الحزبيين.
"ቡድንተኛ ሰው አምስት ፊት ሊኖረው ዝግጁ ነው። ነብዩ ﷺ 'ከክፉ ሰዎች ውስጥ የሆነው ባለ ሁለት ፊት ነው። ያ እነዚያ ዘንድ በአንድ ፊት፣ ሌሎቹን ደግሞ በሌላ ፊት የሚቀርበው።' ሱኒይ የሆነ ሰው ግን እከሌ ቢወድም ሆነ ቢጠላ ዲኑን አጥብቆ የሚይዝ ነው። ከቡድንተኞች በተለየ።" [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 290]

2ኛው ምርጫ፦ ከነዚህ ሲያወድሳቸው ከነበሩ አካላት መለያየቱን ማወጅ ነው። እንደለመዱት ከሙብተዲዕ ጋር የሚቀማመጡ፣ ህብረት የሚፈጥሩ፣ ሰለፊዮችን የሚገፉ፣ ለሙብተዲዕ የሚከላከሉ ሙብተዲዎች ናቸው የሚል መግለጫ ማውጣት። ሰውየው ተቃራኒ ነገሮችን ባንድ ላይ የማስተናገድ ልምድ ቢኖረውም ይሄኛው ግን ለመሸፈን የሚመች አይደለም። "ግመል ሰርቆ አጎንብሶ" የማይሆን ነገር ነው። ስለዚህ መለያየትን ከማወጅ ውጭ ምርጫ አይኖርም። ይህ ሲሆን ደግሞ ህብረቱ ይናዳል።

ካ'ህያ ቆዳ የተሰራ ቤት
ይበታተናል ጅብ የጮኸ 'ለት!

የነዚህ ሰዎች ጉድ ይሄ ብቻ አይደለም። አለ ገና!
ستُبْدي لكَ الأيّامُ ما كنتَ جاهلاً - ويأتِيكَ بالأخبارِ مَن لم تُزَوِّدِ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
* ሰበብ እየፈለገ ሌሎችን ከሱና የሚያስወጣ አካል መጨረሻ ላይ ሌሎችን ባስወጣበት በር ራሱ ይወጣል።
* እወቅ! ሌሎች ላይ የመዘዝከው የኢልዛም ሰይፍ ወዳንተም ይዞራል። እቆርጥበታለሁ ያልከው ይቆርጥሃል።
* ሰለፊያ የወደድከውን የምታስገባበት፣ የጠላሀውን የምታስወጣበት ያ'ባትህ ግቢ አይደለም። ሰለፊያ ኢስላም ማለት እንጂ ሌላ ቡድን አይደለም። ይህንን ከቃላት ባሻገር በተግባር አስረግጥ።
* በዚህ ዘመን በመንሀጅ ስም ተጠቅልሎ ያለው አብዛኛው ጩኸት የአመል ችግር ነው። ያለበለዚያ ሰው እንዴት እስ'ካፍንጫው በተነከረበት ጥፋት ሌሎችን ሊከስ ይደፍራል?
* በሺርክና በቢድዐ መፈረጅ ከሺርክና ከቢድዐ የማስጠንቀቅ ያህል ቀላል አይደለም። ሁለተኛው ላይ ካለህ ትጋት ይልቅ የመጀመሪያውን መድፈርህ መታመምህን ነው የሚያሳየው። ሳይጠናብህ ታከመው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
ቻናሌ ላይ በተደጋጋሚ ማስታወቂያ እየተለቀቀ እንደሆነ አሁን አንድ ወንድም አሳወቀኝ። በራሱ በቴሌግራም እንጂ እኔ እያሰራጨሁት እንዳልሆነ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ። ቀደም ብዬ ያልጠቆምኩት ማስታወቂያው ለኔ ስለማይታየኝ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://hottg.com/IbnuMunewor
አንድ ነጥብ ለአስተውሎት
~
በጣም ከምንሸወድባቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ በእውቀት የሚበልጡንን መሻይኾች ልንጠቀምባቸው አለመቻላችን ነው። በሃገራችን የመንሃጅ ግንዛቤ በጣም የሳሳ እንደሆነ ማንም የማይክደው ሐቅ ነው። ይሄ ክፍተት ደግሞ ብዙ መሻይኾች ላይ ይጎላል። ለወቅታዊ ኪታቦችና ለኢንተርኔት የቀረበው ወጣት #አንፃራዊ በሆነ መልኩ ትንሽ ሻል የሚልበት ሁኔታ አለ። በንፅፅር ነው እያወራሁ ያለሁት። ትንሽ እውቀት የራሱ ብዙ ድክመት አለበትና የማንክደው ብዙ ጣጣ እያመጣብን ነው። ሌሎችን ችግሮች ለጊዜው ልተውና በተነሳሁበት ጉዳይ ላይ ያለውን ላንሳ። ድርቅና (ዒናድ) ሳይሆን የግንዛቤ ችግር ያለባቸውን መሻይኾች መቅረብ እንጂ መራቅ ለሁሉም አይበጅም። ይሄ ማግለልና መግፋት ለነሱም፣ ለኛም፣ ለቆምንለት አላማም፣ ለወገናችንም የሚበጅ አይደለም፡፡ እና ተውሒድና ሱናን መውደድ፣ የሱና ዑለማዎችን ማክበር፣ ለደሊል እጅ መስጠት ካሸተትንባቸው ክፍተቶችን ብናይ እንኳ ከመራቅ ይልቅ መቅረባችን ነው የሚያተርፈን።

1ኛ:- ለነሱም ውለታ መዋል ነው። እኛ ችላ ስንላቸው በሌሎች ይጠለፋሉ። ይሄ ከዚህ ቀደም በስፋት ተከስቷል። እኛ ስንርቃቸው የሌሎች ሲሳይ ሆነዋል። በራሳችን ላይ ጠላት አብዝተናል። ካለፈው ልንማር በቃ ልንል ይገባል፡፡
2ኛ:- ለሰፊው ህዝበ ሙስሊም፦ እነዚህ መሻይኾች ህዝብ ዘንድ የተሻለ ቦታ ስለሚኖራቸው የነሱ መጠንከር ለህዝብ ይተርፋል፡፡ እኛ ባግባቡ ካልቀረብናቸው ግን ሌሎች አካላት የሱናን ደዕዋ በጥላቻና በስጋት እንዲመለከቱ አድርገው ይሞሏቸዋል። ይሄ ደግሞ ዞሮ ዞሮ ዳፋው ለህዝብ ነው የሚተርፈው።
3ኛው:- ጥቅም ለራሳችን ነው፡፡ እኛ ትንሽዬ የመንሃጅ ግንዛቤ አለችን ማለት (ያውም ከኖረ) ከነሱ በእውቀት በለጥን ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ከነጭራሹ እውቀት አለን ማለትም አይደለም። እነሱ ዘንድ መንሃጅ ላይ የግንዛቤ ክፍተት መታየቱ እውቀት የላቸውም ማለት አይደለም፡፡ ለሁለቱም ወገን የሚበጀው መቀራረቡ ነው። እነሱ ዘንድ ያለውን ክፍተት ከቻልን ኪታብ እየገዛንላቸው ፣ ካልሆነ እያዋስናቸው፣ የታላላቅ ዑለማዎችን ንግግር እያሰማናቸው፣ በአደብ እየተከራከርናቸው ለመሙላት መጣር አለብን። በተለይ ኪታብ መስጠት ያለው ዋጋ ቀላል አይደለምና በዚህ ላይ ልንረባረብ ይገባል። የኛን ጅህልና ደግሞ ቁጭ ብሎ በመማር መግፈፍ አለብን። ይህን ስናደርግ ለራሳችንም፣ ለመሻይኾቹም፣ ለወገናችንም ትልቅ ውለታ እንውላለን። ለደዕዋችን መፋፋትም ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ የማወራው ከላይ እንደገለፅኩት ተውሒድና ሱናን መውደድ፣ የሱና ዑለማዎችን ማክበር፣ ለደሊል ራስን ዝቅ ማድረግ፣ ቅንነት ስለሚታይባቸው መሻይኾች ነው።
መቼም በርካታ መሻይኾችና ዱዓቶች ተሰውፍ እና ሌሎችም የተሳሳተ መስመር ውስጥ ከቆዩ በኋላ እንደተመለሱ ይታወቃል። ከአላህ በኋላ ለዚህ መመለሳቸው የተለያዩ ሰበቦች ይኖራሉ። ዛሬም እነዚህን ሰበቦች ችላ ልንላቸው አይገባም። ዛሬም ክፍተት ያለባቸው ሰዎች ሲገጥሙን በመወያየት፣ መረጃ በመለዋወጥ፣ በችግራቸው ከጎናቸው በመቆም ልናቀርባቸው ይገባል። አንተ ትላንት በተለያዩ መስመሮች ላይ አልፈህ መጥተህ ሌሎች ወደሱና እንዳይገቡ በር ለመከርቸም አትታገል። ያለፍክባቸውን አባጣ ጎባጣ መንገዶች መለስ ብለህ አስተውላቸው።
=

ግንቦት 28/2013

https://hottg.com/IbnuMunewor
ጠፍቶ የነበረው ወንድም ተገኝቷል አልሐምዱሊላህ። ሰበብ የሆናችሁ ጀዛኩሙላሁ ኸይረን።
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሒ ወበረካቱሁ ይህ ወንድማችን ወሎ ቦረና ከላላ ወረዳ ልጓማ የምትባል አካባቢ ተወልዶ ያደገ ነዉ።
ተጨማሪ ስልክ
09 14 36 37 98
ወይንም
09 31 82 91 83

ሼር እያደረጋችሁ።
HTML Embed Code:
2024/05/16 04:53:11
Back to Top