TG Telegram Group & Channel
ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ | United States America (US)
Create: Update:

‹‹ወልድኪ መድኃኔዓለም ዲበ ዕፅ ተቀነወ ዘፄወወ ሕዝበ በደሙ ቤዘወ››
‹‹ልጅሽ መድኃኔዓለም በመስቀል ላይ ተቸነከረ በባርነት የነበረውን ሕዝብ በደሙ ተቤዠ››

አባታችን አዳም በበሊዓ ዕጸ በለስ (ዕጸ በለስ በመብላት) ከአምላኩ ተጣልቶ ከገነት ወጥቶ ጸጋውን አጥቶ ለድካም ለመከራ ከምድረ ፋይድ ገብቶ ባለበት ጊዜ ራሱን ጎድቶ ያነባውን ያለቀሰውን የዕንባ ለቅሶ በደሙ ያቀረበውን የይቅርታ መስዋዕት ፈጣሪው ተመልክቶለት የመጀመሪያውን ከሰው ልጅ ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን ለእርሱ ሰጠው፡፡ ቃል ኪዳኑም ይህ ነበር ‹ዓለም (አንተና ዘርህ) በአንተ ደም አትድንም ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ (ከ5500 ዘመን) ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በደሜ አድንሃለሁ›፡፡
በመሆኑም አዳም የተሰጠውን የተስፋ ቃል በማሰብ በተስፋ ይኖር ጀመር፡፡ ይህ የተገባለት ተስፋ ከአምላኩ ይቅርታን አግኝቶ ‹በእንተ ሔዋን ተአጽወ ኆኅተ ገነት› ‹በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ› እንዲል በበደላቸው ተዘግታ የነበረችው ገነት መከፈትን የምታበስር ታላቅ ተስፋ ነበረች፡፡ከአዳም በኋላ የተነሳው በህገ ልቡና ቀናውን ቢከተል በረከት እየበዛለት እድሜው እየተጨመረለት ጥፋትን ቢከተል እድሜው እያጠረበት ሞቱ እየቀረበበት ያለ ሕግ በልቡና መሪነት ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ግን መልካም የሠራው በጽድቅ ሥራው ገነትን ሊከፍት አልቻለም ነበር፡፡ ምግባሩ ሰናይ ካልሆነው ጋር በሲኦል ይደመር ነበር እንጂ! ምንም ቅሉ ይህ ቢሆንም መልካም ሥራ ሠርተው ያረፉትን ቅዱሳን ጻድቃን ነቢያትን በቸርነቱ በረድኤቱ ይጠብቃቸው ነበር፡፡ ጥላ የፀሐይን ሙቀት እንዲከላከል እንዲሁ ረድኤተ እግዚአብሔር መልካም ስራ የሰሩትን በሲኦል ካለው ስቃይ እና መከራ ይጠብቃቸው ነበር፡፡
እግዚአብሔር ለአዳም የገባውን ቃል በየዘመኑ በተነሱ ነቢያት ተፈፃሚ እንደሚሆን አፍ ከፍቶ ቃል አሣክቶ ንግግር አቅንቶ ሕዝቡን ያፅናና ነበር፡፡ ሕዝቅኤል ነቢይ በዘመኑ “ርኢኩ ኆኅተ በምሥራቅ ኀቱም በዓቢይ መንክር ማኀተም አልቦ ዘቦአ ዘእንበለ እግዚአ ኃያላን” “በታላቅ ቁልፍ የተዘጋች ደጅ በመሥራቅ አየሁ ከኃያላን ጌታ በቀር ወደ እርስዋ ገብቶ የወጣ የለም” /ህዝ 4፡4/ ሲል፣ ነቢዩ ኢሳያስም “ህፃን ተወልደ ለነ ወልድ ተውህበ ለነ” “ህፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሠጥቶናል” /ኢሳ 9፡6/ “ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወትስምዮ ስሙ አማኑኤል” “እነሆ ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች “ /ኢሳ 7፡14/ ፣ እና ሌሎችም ነቢያት ከደቂቀ ነቢያት እንደሚክያስ ያሉ ከአበይት ነቢያት ከላይ ከተጠቀሱት ውጪ እንደ ነቢዩ ዳንኤል ያሉ ነቢያቶች አባታችን መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊትም “ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ ወረከብናሁ ውስተ ዖመ ገዳም” “እነሆ በኤፍራታ ሰማነው በዱር ውስጥም አገኘነው” በማለት ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይታየው ምሣሌ የተነገረው ትንቢት ይፈፅም ዘንድ ጊዜው ሲደርስ ንጽሐ ሥጋ፣ ንስሐ ኀሊና፣ ንጽሐ ነፍስን አስተባብራ በያዘችው አስቀድሞ በሥላሴ ኀሊና በታሰበችው በድንግል ማኀፀን በብሥራተ ገብርኤል አደረ፡፡ ጠባቧ የድንግል ማኀፀን ስፍሕት (ሰፊ) ሆና የሠማይ ስርዓት ተከናወነባት ኋላም እንደ ሠው ስርዓት ፈጣሬ ዓለማት ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ በበረሃ ውስጥ በቤተልሔም ተወለደ /ሉቃ 2/ “ፈቂዶ ይፌውስ ትዝምደ ሰብእ ተገረም በማኀፀነ ድንግል “የሠውን ወገን ያድን ዘንድ ወዶ ፈቅዶ በድንግል ማኀፀን አደረ” እንዲል ትምህርተ ኀብአት በተጨማሪ “ሥጋ ለብሰ ዘይማስን ወዘኢይማስን ለሥጋ መዋቲ ረሰዮ ዘኢይማስን” “የማይፈርሰው የሚፈርሰው ሥጋ ለበስ የሚሞተው ሥጋ እንዳይሞት /እንዳይፈርስ/ አደረገው” ተብሎ እንደተፃፈ (በትምህርት ኀቡአት)፡፡አባታችን ቅዱስ ያሬድም በአንቀጸ ብርሃን “እንዘ አልቦቱ እም በሰማያት ወአብ በዲበ ምድር “በሠማይ እናት በምድር ደግሞ አባት የለውም” በማለት ሁለተኛ ልደቱ ያለ አባት መሆኑን ይገልፃል ጌታችን ከወላዲተ አምላክ ከድንግል ሥጋን ከነሣ በኋላ /ከተወለደ በኋላ/ እንደ ህፃናት እየተጫወተ እየተማረ ከኃጢአት በስተቀር የሠውን ስርአት ሁሉ ፈፅሟል፡፡ ‹ወኮነ ሰብአ ከማነ ዘእንበለ ኃጢአት በህቲታ› “ከኃጢአት በቀር እንደ እኛ ሰው ሆነ› እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም /ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ/ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዕብራውያንን ህግ ተምሮ በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ አርባ ቀንና ሌሊት ፆሞ ብዙ ተአምራትን ፈፅሟል፡፡ ይህንን ሲገልፅ ሊቁ ቅዱስ ሕርያቆስ እንዲህ አለ ‹ፍጹመ ኮነ ሰብአ ወኩሎ ሕገ ሰብአ ፈጸመ ዘእንበለ ኃጢአት› ‹ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ሕግ ፈፀመ ‹እምኀበ ዮሐንስ ተጠምቀ ውስተ ገዳም ተመከረ ርኀበ ወጸምአ ወተአምራት ገብረ› ‹ፍፁም ሰው ሆነ ከኃጢአት በስተቀር የሠውን ህግ ፈፀመ የዕብራውያንን ሕግ ተማረ ከዮሐንስ ዘንድ ተጠመቀ በበረሀ ተፈተነ ››/ቅዳሴ ማርያም/
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ነፃ የሚያወጣበት ራሱን አሣልፎ የሚሠጥበት ጊዜ ከመድረሱ አሰቀድሞ በዕለተ ሐሙስ ምሽት መድኃኒት የሚሆን ሥጋውና ደሙን ለዓለም ሠጥቷል፡፡ ስርዓተ ቁርባንን ሠርቷል፡፡ /ማቴ 26፡26/ ይህንን ሥርዓት ከሠራ በኋላም አይሁድ ተሰብስበው ሊይዙት ገመድ ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መጡ፡፡ ‹‹ዘይሰሰይ አክልየ አንስአ ሰኰናሁ በላዕሌየ› ‹እንጀራዬን የበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ /መዝ 40፡9/ እንዳለ ቅዱስ ዳዊት፣ ያስተምረው የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ በ30 ብር አሳልፎ ሠጠው አይሁደም፣ < አምላክ ነኝ ይላል>፣ ፣ ፣ የሰንበትን ቀን ሽሯል በሚሉ የሐሰት ሀሳቦች ተነሥተው ከተያዘበት ሠዓት ጀምረው ያሰቃዩት ነበር፡፡ ሲነጋም በሐሰት ክስ አስፈርደውበት ሊቀጡት በጲላጦስ ፊት አቆሙት፡፡ ‹ሰላም ለአዕጋሪከ እለ ጠብዓ ለቀዊም ቅድመ ጲላጦስ መስፍነ ይሁዳ ወሮም› ‹በሮም እና በይሁዳ መስፍን በጲላጦስ ፊት ያለ ፍርሃት በድፍረት ለቆሙ እግሮችህ ሠላም እላለሁ> እንዲል /መልክዓ ኢየሱስ/›፡፡ የይሁዳ እና የሮም መስፍን የሆነው ጲላጦስ በደል ባያገኝበት የሕዝቡን ዓመፅ ፈርቶ አንደ ፈቃዳቸው ፈረደላቸው አይሁድም እየገፉ፣ እያዳፉ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ አወጡት፡፡ በዕለተ አርብ 6፡00 ሰዓት በሆነም ጊዜ እጆቹን እግሮቹን ቸነከሩት በመስቀል ላይ ሰቀሉት ከገረፉት ግርፋትም የተነሳ ሥጋው አልቆ አጥንቶቹ ይታዩ ነበር (ድርሳነ ማኅየዊ)፡፡ በመዝ 21 ላይ ‹‹ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ማኀበረ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ፣ ወኆለቁ ኩሎ አዕፅምትየ›› ‹‹ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼን እግሮቼን ቸነከሩኝ አጠንቶቼ ሁሉ ተቆጠሩ›› ተብሎ በቅዱስ ዳዊት እንደተነገረ ጌታችን አዳም እፀ በለስን ስለመብላቱ ጌታ በአፍ ሀሞት ተጐነጨ፣ ይህንን ሁሉ መከራ ስለ አዳም ተቀበለ በጠቅላላው 13 ሕማማትን ስለ ሠው ልጆች ተሸከመ፡፡ በቅዳሴ እግዚእ ላይ “ሰፍሐ እደዊሁ ለሕማም ሐመ ከመ ሕሙማን ያድኀን እለ ተወከሉ በላዕሌሁ” ‹‹እጆቹን ለሕማም ዘረጋ በእርሱ የታመኑትን ያድን ዘንድ አንደ ሕሙማን ታመመ›› ተብሎ እንደተፃፈ፡፡

‹‹ወልድኪ መድኃኔዓለም ዲበ ዕፅ ተቀነወ ዘፄወወ ሕዝበ በደሙ ቤዘወ››
‹‹ልጅሽ መድኃኔዓለም በመስቀል ላይ ተቸነከረ በባርነት የነበረውን ሕዝብ በደሙ ተቤዠ››

አባታችን አዳም በበሊዓ ዕጸ በለስ (ዕጸ በለስ በመብላት) ከአምላኩ ተጣልቶ ከገነት ወጥቶ ጸጋውን አጥቶ ለድካም ለመከራ ከምድረ ፋይድ ገብቶ ባለበት ጊዜ ራሱን ጎድቶ ያነባውን ያለቀሰውን የዕንባ ለቅሶ በደሙ ያቀረበውን የይቅርታ መስዋዕት ፈጣሪው ተመልክቶለት የመጀመሪያውን ከሰው ልጅ ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን ለእርሱ ሰጠው፡፡ ቃል ኪዳኑም ይህ ነበር ‹ዓለም (አንተና ዘርህ) በአንተ ደም አትድንም ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ (ከ5500 ዘመን) ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በደሜ አድንሃለሁ›፡፡
በመሆኑም አዳም የተሰጠውን የተስፋ ቃል በማሰብ በተስፋ ይኖር ጀመር፡፡ ይህ የተገባለት ተስፋ ከአምላኩ ይቅርታን አግኝቶ ‹በእንተ ሔዋን ተአጽወ ኆኅተ ገነት› ‹በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ› እንዲል በበደላቸው ተዘግታ የነበረችው ገነት መከፈትን የምታበስር ታላቅ ተስፋ ነበረች፡፡ከአዳም በኋላ የተነሳው በህገ ልቡና ቀናውን ቢከተል በረከት እየበዛለት እድሜው እየተጨመረለት ጥፋትን ቢከተል እድሜው እያጠረበት ሞቱ እየቀረበበት ያለ ሕግ በልቡና መሪነት ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ግን መልካም የሠራው በጽድቅ ሥራው ገነትን ሊከፍት አልቻለም ነበር፡፡ ምግባሩ ሰናይ ካልሆነው ጋር በሲኦል ይደመር ነበር እንጂ! ምንም ቅሉ ይህ ቢሆንም መልካም ሥራ ሠርተው ያረፉትን ቅዱሳን ጻድቃን ነቢያትን በቸርነቱ በረድኤቱ ይጠብቃቸው ነበር፡፡ ጥላ የፀሐይን ሙቀት እንዲከላከል እንዲሁ ረድኤተ እግዚአብሔር መልካም ስራ የሰሩትን በሲኦል ካለው ስቃይ እና መከራ ይጠብቃቸው ነበር፡፡
እግዚአብሔር ለአዳም የገባውን ቃል በየዘመኑ በተነሱ ነቢያት ተፈፃሚ እንደሚሆን አፍ ከፍቶ ቃል አሣክቶ ንግግር አቅንቶ ሕዝቡን ያፅናና ነበር፡፡ ሕዝቅኤል ነቢይ በዘመኑ “ርኢኩ ኆኅተ በምሥራቅ ኀቱም በዓቢይ መንክር ማኀተም አልቦ ዘቦአ ዘእንበለ እግዚአ ኃያላን” “በታላቅ ቁልፍ የተዘጋች ደጅ በመሥራቅ አየሁ ከኃያላን ጌታ በቀር ወደ እርስዋ ገብቶ የወጣ የለም” /ህዝ 4፡4/ ሲል፣ ነቢዩ ኢሳያስም “ህፃን ተወልደ ለነ ወልድ ተውህበ ለነ” “ህፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሠጥቶናል” /ኢሳ 9፡6/ “ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወትስምዮ ስሙ አማኑኤል” “እነሆ ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች “ /ኢሳ 7፡14/ ፣ እና ሌሎችም ነቢያት ከደቂቀ ነቢያት እንደሚክያስ ያሉ ከአበይት ነቢያት ከላይ ከተጠቀሱት ውጪ እንደ ነቢዩ ዳንኤል ያሉ ነቢያቶች አባታችን መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊትም “ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ ወረከብናሁ ውስተ ዖመ ገዳም” “እነሆ በኤፍራታ ሰማነው በዱር ውስጥም አገኘነው” በማለት ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይታየው ምሣሌ የተነገረው ትንቢት ይፈፅም ዘንድ ጊዜው ሲደርስ ንጽሐ ሥጋ፣ ንስሐ ኀሊና፣ ንጽሐ ነፍስን አስተባብራ በያዘችው አስቀድሞ በሥላሴ ኀሊና በታሰበችው በድንግል ማኀፀን በብሥራተ ገብርኤል አደረ፡፡ ጠባቧ የድንግል ማኀፀን ስፍሕት (ሰፊ) ሆና የሠማይ ስርዓት ተከናወነባት ኋላም እንደ ሠው ስርዓት ፈጣሬ ዓለማት ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ በበረሃ ውስጥ በቤተልሔም ተወለደ /ሉቃ 2/ “ፈቂዶ ይፌውስ ትዝምደ ሰብእ ተገረም በማኀፀነ ድንግል “የሠውን ወገን ያድን ዘንድ ወዶ ፈቅዶ በድንግል ማኀፀን አደረ” እንዲል ትምህርተ ኀብአት በተጨማሪ “ሥጋ ለብሰ ዘይማስን ወዘኢይማስን ለሥጋ መዋቲ ረሰዮ ዘኢይማስን” “የማይፈርሰው የሚፈርሰው ሥጋ ለበስ የሚሞተው ሥጋ እንዳይሞት /እንዳይፈርስ/ አደረገው” ተብሎ እንደተፃፈ (በትምህርት ኀቡአት)፡፡አባታችን ቅዱስ ያሬድም በአንቀጸ ብርሃን “እንዘ አልቦቱ እም በሰማያት ወአብ በዲበ ምድር “በሠማይ እናት በምድር ደግሞ አባት የለውም” በማለት ሁለተኛ ልደቱ ያለ አባት መሆኑን ይገልፃል ጌታችን ከወላዲተ አምላክ ከድንግል ሥጋን ከነሣ በኋላ /ከተወለደ በኋላ/ እንደ ህፃናት እየተጫወተ እየተማረ ከኃጢአት በስተቀር የሠውን ስርአት ሁሉ ፈፅሟል፡፡ ‹ወኮነ ሰብአ ከማነ ዘእንበለ ኃጢአት በህቲታ› “ከኃጢአት በቀር እንደ እኛ ሰው ሆነ› እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም /ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ/ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዕብራውያንን ህግ ተምሮ በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ አርባ ቀንና ሌሊት ፆሞ ብዙ ተአምራትን ፈፅሟል፡፡ ይህንን ሲገልፅ ሊቁ ቅዱስ ሕርያቆስ እንዲህ አለ ‹ፍጹመ ኮነ ሰብአ ወኩሎ ሕገ ሰብአ ፈጸመ ዘእንበለ ኃጢአት› ‹ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ሕግ ፈፀመ ‹እምኀበ ዮሐንስ ተጠምቀ ውስተ ገዳም ተመከረ ርኀበ ወጸምአ ወተአምራት ገብረ› ‹ፍፁም ሰው ሆነ ከኃጢአት በስተቀር የሠውን ህግ ፈፀመ የዕብራውያንን ሕግ ተማረ ከዮሐንስ ዘንድ ተጠመቀ በበረሀ ተፈተነ ››/ቅዳሴ ማርያም/
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ነፃ የሚያወጣበት ራሱን አሣልፎ የሚሠጥበት ጊዜ ከመድረሱ አሰቀድሞ በዕለተ ሐሙስ ምሽት መድኃኒት የሚሆን ሥጋውና ደሙን ለዓለም ሠጥቷል፡፡ ስርዓተ ቁርባንን ሠርቷል፡፡ /ማቴ 26፡26/ ይህንን ሥርዓት ከሠራ በኋላም አይሁድ ተሰብስበው ሊይዙት ገመድ ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መጡ፡፡ ‹‹ዘይሰሰይ አክልየ አንስአ ሰኰናሁ በላዕሌየ› ‹እንጀራዬን የበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ /መዝ 40፡9/ እንዳለ ቅዱስ ዳዊት፣ ያስተምረው የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ በ30 ብር አሳልፎ ሠጠው አይሁደም፣ < አምላክ ነኝ ይላል>፣ ፣ ፣ የሰንበትን ቀን ሽሯል በሚሉ የሐሰት ሀሳቦች ተነሥተው ከተያዘበት ሠዓት ጀምረው ያሰቃዩት ነበር፡፡ ሲነጋም በሐሰት ክስ አስፈርደውበት ሊቀጡት በጲላጦስ ፊት አቆሙት፡፡ ‹ሰላም ለአዕጋሪከ እለ ጠብዓ ለቀዊም ቅድመ ጲላጦስ መስፍነ ይሁዳ ወሮም› ‹በሮም እና በይሁዳ መስፍን በጲላጦስ ፊት ያለ ፍርሃት በድፍረት ለቆሙ እግሮችህ ሠላም እላለሁ> እንዲል /መልክዓ ኢየሱስ/›፡፡ የይሁዳ እና የሮም መስፍን የሆነው ጲላጦስ በደል ባያገኝበት የሕዝቡን ዓመፅ ፈርቶ አንደ ፈቃዳቸው ፈረደላቸው አይሁድም እየገፉ፣ እያዳፉ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ አወጡት፡፡ በዕለተ አርብ 6፡00 ሰዓት በሆነም ጊዜ እጆቹን እግሮቹን ቸነከሩት በመስቀል ላይ ሰቀሉት ከገረፉት ግርፋትም የተነሳ ሥጋው አልቆ አጥንቶቹ ይታዩ ነበር (ድርሳነ ማኅየዊ)፡፡ በመዝ 21 ላይ ‹‹ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን ማኀበረ ለእኩያን ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ፣ ወኆለቁ ኩሎ አዕፅምትየ›› ‹‹ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼን እግሮቼን ቸነከሩኝ አጠንቶቼ ሁሉ ተቆጠሩ›› ተብሎ በቅዱስ ዳዊት እንደተነገረ ጌታችን አዳም እፀ በለስን ስለመብላቱ ጌታ በአፍ ሀሞት ተጐነጨ፣ ይህንን ሁሉ መከራ ስለ አዳም ተቀበለ በጠቅላላው 13 ሕማማትን ስለ ሠው ልጆች ተሸከመ፡፡ በቅዳሴ እግዚእ ላይ “ሰፍሐ እደዊሁ ለሕማም ሐመ ከመ ሕሙማን ያድኀን እለ ተወከሉ በላዕሌሁ” ‹‹እጆቹን ለሕማም ዘረጋ በእርሱ የታመኑትን ያድን ዘንድ አንደ ሕሙማን ታመመ›› ተብሎ እንደተፃፈ፡፡


>>Click here to continue<<

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)