የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ሊሻሻል መሆኑ ተገለፀ!
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረውን የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል። ረቂቅ አዋጁ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍም ተወስኗል።
ይህ ማሻሻያ አሁን ካለዉ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ፣ በነበረው አዋጅ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች ለመድፈን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ የግብር ስርዓቱ መሰረታዊ የግብር መርሆችን (ታክስ ፕሪንሲፕልስ) የሚያሳካ በሚያስችል መልኩ እንዲቀረጽ መደረጉ ታውቋል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
>>Click here to continue<<
