TG Telegram Group & Channel
YeneTube | United States America (US)
Create: Update:

እስራኤል ለ60 ቀናት በጋዛ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቷን ትራምፕ አስታወቁ!

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል በጋዛ የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነትን ለማድረግ "አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን" ለማሟላት ተስማምታለች ሲሉ ተናገሩ።

ፕሬዚደንቱ በትሩዝ የማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ እንደጻፉት ከሆነ በምክረ ሃሳቡ ስምምነት ወቅት "ጦርነቱን ለማቆም ከሁሉም አካላት ጋር እንሰራለን" ያሉ ሲሆን ቅድመ ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

"ሰላም ለማምጣት በጣም ጠንክረው የሠሩት ኳታራውያን እና ግብፃውያን የመጨረሻውን ምክረ ሀሳብ ያቀርባሉ። . . . ሃማስ ይህንን ስምምነት ይቀበላል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ምክንያቱም የተሻለ አይሆንም፤ እየባሰ ነው የሚሄደው" ሲሉ ትራምፕ ጽፈዋል።

መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቀቃት ፈጽሞ 1,200 ሰዎችን ከገደለ በኋላ እስራኤል በጋዛ ወታደራዊ ዘመቻዋን ጀምራለች።

በግዛቱ በሐማስ የሚመራ የጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቢያንስ 56,647 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa

እስራኤል ለ60 ቀናት በጋዛ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቷን ትራምፕ አስታወቁ!

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል በጋዛ የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነትን ለማድረግ "አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን" ለማሟላት ተስማምታለች ሲሉ ተናገሩ።

ፕሬዚደንቱ በትሩዝ የማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ እንደጻፉት ከሆነ በምክረ ሃሳቡ ስምምነት ወቅት "ጦርነቱን ለማቆም ከሁሉም አካላት ጋር እንሰራለን" ያሉ ሲሆን ቅድመ ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

"ሰላም ለማምጣት በጣም ጠንክረው የሠሩት ኳታራውያን እና ግብፃውያን የመጨረሻውን ምክረ ሀሳብ ያቀርባሉ። . . . ሃማስ ይህንን ስምምነት ይቀበላል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ምክንያቱም የተሻለ አይሆንም፤ እየባሰ ነው የሚሄደው" ሲሉ ትራምፕ ጽፈዋል።

መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቀቃት ፈጽሞ 1,200 ሰዎችን ከገደለ በኋላ እስራኤል በጋዛ ወታደራዊ ዘመቻዋን ጀምራለች።

በግዛቱ በሐማስ የሚመራ የጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቢያንስ 56,647 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
16😭6😁21👎1👀1


>>Click here to continue<<

YeneTube






Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)