TG Telegram Group & Channel
YeneTube | United States America (US)
Create: Update:

የመንግስታቱ ድርጅት በአማራ ክልል የረድኤት ሰራተኛ መገደሏን ተከትሎ ድርጊቱን አወገዘ፣ የረድኤት ድርጅት ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋል!

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን “አንጎት” ወረዳ “በመንግስት ሃይሎች እና በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መካከል” ተከስቶ በነበረው ግጭት በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስላ የነበረች የረድኤት ድርጅት ሰራተኛ ማህሌት ስጦታው አበራ መሞቷን አስታውቋል፤ ድርጊቱንም አውግዟል።

የማስተባበሪያ ቢሮው ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማህሌት “በተኩስ ልውውጡ ጉዳት የደረሰባት በአከባቢው የእርዳታ እህል አቅርቦት የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች በተመለከተ መረጃ እያሰባሰበች፣ በስራ ላይ በነበረችበት ወቅት ነው” ብሏል።

ሃላፊዋ አቢባቶ ዋነ-ፎል ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ባልደረቦቿ ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ “የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን የማስተላልፈው ለሟች ቤተሰብ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ የሰብአዊ ረድኤት ሰራተኞች ነው” ሲሉ ገልጸዋል፤ “ንጹሃንን እና ለተቸገሩ ሰዎች እርዳታ ለማቅረብ የሚጥሩ ሰራተኞችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሁሉም እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል ብለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa

የመንግስታቱ ድርጅት በአማራ ክልል የረድኤት ሰራተኛ መገደሏን ተከትሎ ድርጊቱን አወገዘ፣ የረድኤት ድርጅት ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋል!

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን “አንጎት” ወረዳ “በመንግስት ሃይሎች እና በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መካከል” ተከስቶ በነበረው ግጭት በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስላ የነበረች የረድኤት ድርጅት ሰራተኛ ማህሌት ስጦታው አበራ መሞቷን አስታውቋል፤ ድርጊቱንም አውግዟል።

የማስተባበሪያ ቢሮው ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማህሌት “በተኩስ ልውውጡ ጉዳት የደረሰባት በአከባቢው የእርዳታ እህል አቅርቦት የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች በተመለከተ መረጃ እያሰባሰበች፣ በስራ ላይ በነበረችበት ወቅት ነው” ብሏል።

ሃላፊዋ አቢባቶ ዋነ-ፎል ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ባልደረቦቿ ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ “የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን የማስተላልፈው ለሟች ቤተሰብ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ የሰብአዊ ረድኤት ሰራተኞች ነው” ሲሉ ገልጸዋል፤ “ንጹሃንን እና ለተቸገሩ ሰዎች እርዳታ ለማቅረብ የሚጥሩ ሰራተኞችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሁሉም እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል ብለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
14😭8👎1😁1


>>Click here to continue<<

YeneTube






Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)