TG Telegram Group & Channel
YeneTube | United States America (US)
Create: Update:

በመንግስት ግዥ ሂደት ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች የይግባኝ ዉሳኔ ቢያገኙም ዉሳኔዉ ተፈፃሚ እየሆነ አይደለም ተባለ!

አንዳንድ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በይግባኝ ቦርዱ የሚሰጣቸዉን የይግባኝ ዉሳኔ እንደማይተገብሩ ተገልፆል።የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በበጀት አመቱ 148 ይግባኝ እንደቀረበ አስታዉቋል።

ከቀረቡት ዉስጥ መረጃ ተሟልቶ ለቀረቡ ምርመራ በማድረግ ለ 142 የይግባኝ ጥያቄዎች ዉሳኔ መሰጠቱን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ተናግረዋል።የይግባኝ ጥያቄዉ በግዥ አፈፃፀም እና ንብረት ሽያጭ ላይ የመንግሥት መስሪያ ቤቱ የሕግ ጥሰት አለበት ብሎ የሚያምን ተወዳዳሪ ወይም ተጫራች እንዲመረመርለት የሚያቀርበዉ ቅሬታ ነዉ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሆኖም የቦርዱን የይግባኝ ዉሳኔ ተቀበሎ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳሉ ገልፀዋል።መስሪያ ቤቶቹ የይግባኝ ቦርዱ የተቋቋመዉ በአዋጅ እንደመሆኑ የተሰጠዉን ዉሳኔ መቀበል ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።

አያይዘዉም በይግባኝ የተሰጡ ዉሳኔዎች አተገባበር ላይ በልዩ ሁኔታ ኦዲት ተደርጎ ሪፖርት እንዲወጣ ለማድረግ መታሰቡንም ጠቁመዋል።የመንግስት ግዢ እና ንብረት አስተዳደር በህጉ መሠረት መከወኑን ለመለየት 62 ተቋማት ላይ የህጋዊነት ኦዲት መደረጉን የመንግስት ግዢ እና ንብረት ባለስልጣን አሳዉቋል።ባለስልጣኑ የበጀት አመቱን ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት በ 16 የመንግስት ተቋማት ላይ የኦዲት ጥቆማ እንደቀረበለት ሰምተናል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa

በመንግስት ግዥ ሂደት ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች የይግባኝ ዉሳኔ ቢያገኙም ዉሳኔዉ ተፈፃሚ እየሆነ አይደለም ተባለ!

አንዳንድ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በይግባኝ ቦርዱ የሚሰጣቸዉን የይግባኝ ዉሳኔ እንደማይተገብሩ ተገልፆል።የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በበጀት አመቱ 148 ይግባኝ እንደቀረበ አስታዉቋል።

ከቀረቡት ዉስጥ መረጃ ተሟልቶ ለቀረቡ ምርመራ በማድረግ ለ 142 የይግባኝ ጥያቄዎች ዉሳኔ መሰጠቱን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ተናግረዋል።የይግባኝ ጥያቄዉ በግዥ አፈፃፀም እና ንብረት ሽያጭ ላይ የመንግሥት መስሪያ ቤቱ የሕግ ጥሰት አለበት ብሎ የሚያምን ተወዳዳሪ ወይም ተጫራች እንዲመረመርለት የሚያቀርበዉ ቅሬታ ነዉ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሆኖም የቦርዱን የይግባኝ ዉሳኔ ተቀበሎ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳሉ ገልፀዋል።መስሪያ ቤቶቹ የይግባኝ ቦርዱ የተቋቋመዉ በአዋጅ እንደመሆኑ የተሰጠዉን ዉሳኔ መቀበል ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።

አያይዘዉም በይግባኝ የተሰጡ ዉሳኔዎች አተገባበር ላይ በልዩ ሁኔታ ኦዲት ተደርጎ ሪፖርት እንዲወጣ ለማድረግ መታሰቡንም ጠቁመዋል።የመንግስት ግዢ እና ንብረት አስተዳደር በህጉ መሠረት መከወኑን ለመለየት 62 ተቋማት ላይ የህጋዊነት ኦዲት መደረጉን የመንግስት ግዢ እና ንብረት ባለስልጣን አሳዉቋል።ባለስልጣኑ የበጀት አመቱን ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት በ 16 የመንግስት ተቋማት ላይ የኦዲት ጥቆማ እንደቀረበለት ሰምተናል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
22


>>Click here to continue<<

YeneTube






Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)