TG Telegram Group & Channel
YeneTube | United States America (US)
Create: Update:

ኮንጎ እና ሩዋንዳ ለረዥም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ተፈራረሙ!

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ለአስርት ዓመታት የዘለቀውን አስከፊ ግጭት ለማስቆም የሚያስችል የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ተፈራረሙ።በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማካኝነት የተፈረመው ይህ የሰላም ስምምነት አሜሪካ ከኮንጎ ብርቅዬ ማዕድናት ተጠቃሚ እንድትሆን ሊያደርጋት እንደሚችል ተገልጿል።

በሁለቱ ጎረቤት አገራት የተደረሰው የሰላም ስምምነት በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊከ ኮንጎ የሚዋጉ ታጣቂ ቡድኖች "ውጊያ ማቆም፣ ትጥቅ መፍታት እና ተዋጊዎችን ወደ መደበኛ ሕይወት መመለስን ያለመ" ነው።ስምምነቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎች አልወጡም።

በቀጠናው አሸማጋይነት የተጀመሩ የሰላም ስምምነቶች ከዚህ ቀደም ቢከሽፉም የአሜሪካ እና የኮንጎ መሪዎች ስምምነቱን ከአሁኑ "ትልቅ ድል" ሲሉ አሞካሽተውታል።"ዛሬ ግጭቱ እና ውድመቱ ተቋጭቷል።መላው ቀጠና አዲስ የተስፋ እና የእድል ምዕራፍ ጀምሯል" ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አርብ ዕለት ተናግረዋል።

ትራምፕ፤ ምክትል ፕሬዚዳንታቻው ጄዲ ቫንስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ማርኮ ሩቢዮ እንዲሁም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ የተውጣጡ ልዑካን በተገኙበት ቢሯቸው በሰጡት መግለጫ የሰላም ስምምነቱን "አስደናቂ ድል" ብለውታል።ስምምነቱ የተፈረመው በአገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካኝነት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ ነው።

ትራምፕ ከዚያ በኋላ በስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ባኖሩበት ወቅት "ትልቅ ስኬት ነው" ብለዋል።የኮንጎ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤትም "ለፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኪዲ በ30 ዓመት ከታዩት የበለጠ ሌላ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት " ሲል የሰላም ስምምነቱ ከመፈረሙ በፊት መግለጫ አውጥቷል።

ምንም እንኳን ቀኑ ባይገለጽም የኮንጎው ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኪዲ እና የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ወደ ዋሽንግተን አቅንተው ከትራምፕ ጋር እንደሚገናኙ ተነግሯል።በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ውጥረት በተባባሰበት ወቅት ኳታር ይህንን ለማርገብ ከጥቂት ወራት በፊት የሽምግልና ጥረት መጀመሯን ስለ ድርድሩ የሚያውቁ ዲፕሎማት ተናግረዋል።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa

ኮንጎ እና ሩዋንዳ ለረዥም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ተፈራረሙ!

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ለአስርት ዓመታት የዘለቀውን አስከፊ ግጭት ለማስቆም የሚያስችል የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ተፈራረሙ።በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማካኝነት የተፈረመው ይህ የሰላም ስምምነት አሜሪካ ከኮንጎ ብርቅዬ ማዕድናት ተጠቃሚ እንድትሆን ሊያደርጋት እንደሚችል ተገልጿል።

በሁለቱ ጎረቤት አገራት የተደረሰው የሰላም ስምምነት በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊከ ኮንጎ የሚዋጉ ታጣቂ ቡድኖች "ውጊያ ማቆም፣ ትጥቅ መፍታት እና ተዋጊዎችን ወደ መደበኛ ሕይወት መመለስን ያለመ" ነው።ስምምነቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎች አልወጡም።

በቀጠናው አሸማጋይነት የተጀመሩ የሰላም ስምምነቶች ከዚህ ቀደም ቢከሽፉም የአሜሪካ እና የኮንጎ መሪዎች ስምምነቱን ከአሁኑ "ትልቅ ድል" ሲሉ አሞካሽተውታል።"ዛሬ ግጭቱ እና ውድመቱ ተቋጭቷል።መላው ቀጠና አዲስ የተስፋ እና የእድል ምዕራፍ ጀምሯል" ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አርብ ዕለት ተናግረዋል።

ትራምፕ፤ ምክትል ፕሬዚዳንታቻው ጄዲ ቫንስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ማርኮ ሩቢዮ እንዲሁም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ የተውጣጡ ልዑካን በተገኙበት ቢሯቸው በሰጡት መግለጫ የሰላም ስምምነቱን "አስደናቂ ድል" ብለውታል።ስምምነቱ የተፈረመው በአገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አማካኝነት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ ነው።

ትራምፕ ከዚያ በኋላ በስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ባኖሩበት ወቅት "ትልቅ ስኬት ነው" ብለዋል።የኮንጎ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤትም "ለፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኪዲ በ30 ዓመት ከታዩት የበለጠ ሌላ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት " ሲል የሰላም ስምምነቱ ከመፈረሙ በፊት መግለጫ አውጥቷል።

ምንም እንኳን ቀኑ ባይገለጽም የኮንጎው ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኪዲ እና የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ወደ ዋሽንግተን አቅንተው ከትራምፕ ጋር እንደሚገናኙ ተነግሯል።በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ውጥረት በተባባሰበት ወቅት ኳታር ይህንን ለማርገብ ከጥቂት ወራት በፊት የሽምግልና ጥረት መጀመሯን ስለ ድርድሩ የሚያውቁ ዲፕሎማት ተናግረዋል።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa


>>Click here to continue<<

YeneTube




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)