TG Telegram Group & Channel
ፉርቃን ኦንላይን ቁርኣን ማዕከል | United States America (US)
Create: Update:

ፍልስጤም - የደም ነጋዴዎች ካርድ!
~~~~~~~~~~
የፍልስጤም ወገኖቻችን ሰቆቃ ከወትሮው በጨመረ ቁጥር ይህንን አስታኮ ዑለማዎች ላይ መዝመት የተለመደ ክስተት ሆኗል። ሙስሊሞች ስሜታቸው የተነካበተን ጊዜ ጠብቀው ዑለማዎችን እንዲንቁ በፍርሃትና በሸፍጠኘነት እየወነጀሉ የጥላቻ መርዝ የሚግቱ opportunisቶች አሉ! የኢኽዋን ቫይረስ ተሸካሚዎች አብይ መታወቂያ ይሄ ነው። የሰለፊያ ዑለማዎች ናቸው በፍርሃትና ጂሃድን በመቃወም የሚወነጀሉት? እነ አልባኒ፣ ኢብኑ ባዝ፣ ዑሠይሚን፣... አይደሉ እንዴ ለአፍጋኒስታን ጦርነት ሲቀሰቅሱ የነበሩት? እነ ረቢዕ የአፍጋኒስታን ጂሃድ ላይ አልተሳተፉም ወይ?! ህይወታቸው በነዚህ የጥመት አንጃዎች አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ሐቅን በማድረስ ላይ አልተዋደቁምን? እነ ኢሕሳን ኢለሂ ዞሂር በተጠመደ ቦምብ አልተገደሉም? እነ ጀሚሉ ረሕማን ኩነር አፍጋኒስታን ውስጥ አልተገደሉም? እነ ሙቅቢል መስጂድ ውስጥ ከተጠመደ ቦምብ ለትንሽ አልተረፉም? ለህይወታቸው ቢሳሱ ነው’ንዴ ሌሎች የተሸበቡበትን ርእስ ከፍ በማድረግ ደም የጠማቸው የጥፋት አንጃዎችን የሚጋፈጡት? የኢኽዋን ቆሻሾች እንደሚወነጅሏቸው ፈሪዎች ስለሆኑ ነው በዚህ ደረጃ ህይወታቸው አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ወደኋላ የማይሉት? እነዚህ ሳይሞቅ ፈላዎች ጀግና ከሆኑ ለምን ወደ ፍልስጤም አይዘምቱም? ፍልስጤም ብትርቃቸው እዚሁ አፍሪካ ውስጥ ሙስሊሞች የሚበደሉባቸው በርካታ ሃገራት አሉ’ኮ። ፌስቡክ ላይ ከሚፎክሩ ለምን ነፍጥ አንግበው ጫካ አይገቡም? ሁሌ ከዑለማእ ውስጥ ሰለፊዮቹ ላይ፣ ከሃገራት ውስጥ ሳዑዲ ላይ ነው የሚዘምቱት።
ለእስራኤል የደህንነትና የስለላ መረጃዎችን የሚያቀብለው የኩርጂክ የራዳር ማእከል ቱርክ ውስጥ ነው የሚገኘው። ከእስራኤል ከፍተኛ የንግድ አጋሮች ውስጥ አንዷ ቱርክ ነች። ከሙስሊሙ አለም በቱርክ ደረጃ ለሷ ወዳጅ የሆነ የለም። በቅርቡ ቃጠሎ ሲገጥማት የእሳት ማጥፊያ አውሮፕላኖችን የላከች ቱርክ ነች። “የእስራኤል አባት” ተብሎ የሚጠራው ቴዎዶር ሄርዝል ቀብር ላይ የአበባ ጉንጉን ያስቀመጠው ኤርዶጋን ነው። በተለያዩ ጊዜያት የጋራ የጦር ልምምድ ሲያደርጉ እንደነበር የሚታወቅ ነበር። በዚህ ቀውጢ ጊዜ ሳይቀር በጎን ባዶ የቃላት ኳኳታ እያሰሙ ሲያደነዝዙ፣ በሌላ በኩል የንግድ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር ኢኽዋኖችና የነሱን ተውሳክ የተሸከሙ አካላት ነጋ ጠባ “ሳዑዲ፣ ሳዑዲ” እያሉ ማላዘን ነው የሚቀናቸው። ኢላማቸው መሪዎቹ አይደሉም። ወደ ዑለማዎቹ ለመሻገር ነው የነሱን ጉዳይ የሚያነሱት።
እስኪ አሁን “ጂሃድ በደመ–ነፍስ የሚካሄድ ሳይሆን ዝግጅት ይፈልጋል” የሚል ምክር ምን እንከን ይወጣለታል? ሃሳቡን አይቀበሉ! ምናል በቅንነት ተመልክተው ለሌሎች የሚሰጡትን ‘ዑዝር’ ቢሰጧቸው? እንዴትስ እዝነት መቆርቆራቸው በክፋትና በፍርሃት ይተረጎማል? የቢድዐ ልክፍት ያሳበዳቸው ወፈፌዎች ካልሆኑ በስተቀር ይሄ ጤነኛ አእምሮ ላለው የሚሰወር አይደለም። ቤት ውስጥ በሚዘጋጅ የጠርሙስ ቦምብ ነው ኒኩሌር ከታጠቀ ኃይል ጋር የምትዋጋው? በወፍ ማደኛ ወስፈንጠር ነው ከታንክ ጋር የምትፋለመው? በህልም ነው በውን ክላስተር ቦምብ የሚያዘንቡ ጄቶች በወንጭፍ የሚወርዱት? ለመሆኑ ለምንድን ነበር ሙስሊሞች መካ ላይ እያሉ በጂሃድ ያልታዘዙት? ደካማ ስለነበሩ አይደለምን? መዲና ውስጥ አቅማቸው ሲጠነክር’ኮ ነቢዩን ﷺ የተሳደበ አካል እርምጃ ተወስዶበታል። መካ ሳሉስ? ከስድብ በላይ ብዙ አልደረሰባቸውም? የገማ እንግዴ ልጅ አልተጣለባቸውም? ለምን እርምጃ አልወሰዱም? ምክንያት የለውም’ንዴ? ሶሐቦች ያ ሁሉ ሲደርስባቸው፣ እነ ሱመያ እነ ያሲር ሲገደሉ፣ ሌሎች አገር ጥለው እንዲሰደዱ ያደረጋቸው ግፍ ሲያስተናግዱ የፈለገ ይሁን ብለው አሳቻ ቦታ እየጠበቁ ጥቃት ማድረስ አቅቷቸው አልነበረም’ኮ! ቢላል ክፉኛ ሲያንገላታው የነበረውን ኡመያን ለመግደል ከአመታት በኋላ የተካሄደውን የበድር ዘመቻ ሳይጠብቅ ገና ቁስሉ ሳይደርቅ መካ ውስጥ መግደል አቅቶት’ኮ አልነበረም። ሸሪዐው የጂሃድን ትእዛዝ ያዘገየው ያለ ምክንያት ነው’ንዴ? አቅም እንዲያጎለብቱ፣ ዝግጅት እንዲያደርጉ እንጂ! የላቀው አላህ ምንድነው ያለው?
وَأَعِدُّواْ لَهُم مَّا ٱسۡتَطَعۡتُم مِّن قُوَّةٖ وَمِن رِّبَاطِ ٱلۡخَيۡلِ تُرۡهِبُونَ بِهِۦ عَدُوَّ ٱللَّهِ وَعَدُوَّكُمۡ
“ለእነሱም ከማንኛውም ኃይል (መሳሪያ) እና ከታጀቡ ፈረሶችም የቻላችሁትን ሁሉ በእርሱ የአላህን ጠላትና ጠላታችሁን የምታሸብሩበትን አዘጋጁላቸው።" [አልአንፋል፡ 60]
ሶሐቦቹ ይህንን መለኮታዊ ትእዛዝ ተከትለው ጠላትን የሚገዳደር ዝግጅት አድርገዋል። ዛሬ ወደ ጦር ሜዳ የምትጓዘው በፈረስ፣ የምትወረውረውም ቀስት አይደለም። ጠላት አእላፍ ኪሎ ሜትሮችን ርቆ አንተን ማደባየት ይችላል። ሙስሊሙ የትኛው ዝግጅት ነው ያለው? ምናልባት “የሰለጠኑ ፈረሶችን አዘጋጅተናል” ይሉ ይሆን? አይሉም አይባልም እነዚህ ማስተዋል የተሳናቸው ጉዶች? በዓለም ላይ እጅግ አውዳሚ የሆኑ ሃይድሮጂን ቦምቦች፣ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች፣ ግዙፍ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች፣ ጅምላ ጭራሽ ባዮሎጂካል መሳሪያዎች፣ ከራዳር ቁጥጥር ውጭ የሆኑ የተራቀቁ የጦር አውሮፕላኖች፣ ወዘተ የታጠቁት ሙስሊም ሃገራት አይደሉም። ወደ 16 ሺህ ከሚገመተው የዓለም ኒኩሌር 90 ከመቶ በላይ በአሜሪካና በራሺያ እጅ ነው ያለው። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በጃፓን ሂሮሽማና ናጋሳኪ ከተሞች ላይ 2 መቶ ሺህ አካባቢ ህዝብ ያለቀው በሁለት ኒኩሌር ብቻ ነው። ይህን ያክል ርቀዋል። የዛሬ ሙስሊም ሃገራት የ1945ቷን ጃፓን አያክሉም። ከመሆኑም ጋር ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ ተንኮታኩታ ነበር እጅ የሰጠችው። ጋዳፊን በቀናት ውስጥ ያሽመደመደው የፈረንሳይ አየር ኃይል እንጂ ተቃዋሚዎቹማ እዚህ ግባ የሚባል አቅም አልነበራቸውም። በርካቶች ዘንድ ተጋኖ ተስሎ የነበረው የሳዳም ጦር እንደ ቅቤ የቀለጠው ያለ ምክንያት አይደለም!! “የዐረብ ሃገራት ናቸው ጉድ የሰሩት” እያሉ ዋናውን ምስል መዘንጋት እራስን ማታለል ነው? ወደድንም ጠላንም በመሃላችን ያለው ርቀት ከምንገምተው በላይ እጅግ የሰፋ ነው። 
እጅግ በርካታ “ሙፈኪሮች” ያለንበትን ተጨባጭ በውል አልተረዱም። ምነው ችግሩ በዚህ በቅቶ መከራችን በቀለለ?! በዚህ ሰመመናቸው ውስጥ ሆነው “ፊቅሁል ዋቂዕ አልገባቸውም” እያሉ ዑለማዎች ላይ መዝመታቸው ባሰ እንጂ። የነሱ የጥመት አውራዎች ሲነኩ ግን “ዑለማእ ተሰደበ” እያሉ አገር ያቃጥላሉ። ዑለማዎቻችንን ተውልን። ክፍተት ቢኖራቸው እንኳ እንደ ቀርዷዊ ካሉ የጥፋት ቁንጮዎች ጋር የሚነፃፀሩ አይደሉም። በምን ስሌት ነው እነዚያ እየታለፉ በነዚህ ላይ ሌት ከቀን የሚዘመተው?!
እንዲህ አይነቱ ኸዋሪጅ ጋር እየዋለ፣ የኸዋሪጅ ፊክራ እየጠጣ፣ ኸዋሪጅኛ የሚያስነጥስ የጥጃ ቀንዳም ነገሮችን በውል መመዘን፣ ግራ ቀኝ መመልከት የሚባል አያውቅም። ሙስሊሙ ዓለም ከአሜሪካም፣ ከራሺያም፣ ከፈረንሳይም፣ ከእንግሊዝም፣ ከቻይናም፣ ከህንድም፣ ከእስራኤልም ጋር እንዲዋጋ ነው የሚሹት። ተጨባጩ ግን እንኳን ከነዚህ ሁሉ ቀርቶ አንዱንም በሚቋቋምበት ቁመና ላይ አለመሆኑ ነው። ቱርክ ጦሯን ድንበር ተሻግራ ሶሪያ ውስጥ ብታስገባም "ለሃገሬ ስጋት ናቸው" የምትላቸውን የኩርድ ታጣቂዎች ከማጥቃት ባለፈ በሻረል አሰድን ለመንካት የማትደፍረው ወዳው አይደለም፤ ራሺያን ፈርታ እንጂ። ቻይና “የግዛቴ አካል ናት” የምትላትን

ፍልስጤም - የደም ነጋዴዎች ካርድ!
~~~~~~~~~~
የፍልስጤም ወገኖቻችን ሰቆቃ ከወትሮው በጨመረ ቁጥር ይህንን አስታኮ ዑለማዎች ላይ መዝመት የተለመደ ክስተት ሆኗል። ሙስሊሞች ስሜታቸው የተነካበተን ጊዜ ጠብቀው ዑለማዎችን እንዲንቁ በፍርሃትና በሸፍጠኘነት እየወነጀሉ የጥላቻ መርዝ የሚግቱ opportunisቶች አሉ! የኢኽዋን ቫይረስ ተሸካሚዎች አብይ መታወቂያ ይሄ ነው። የሰለፊያ ዑለማዎች ናቸው በፍርሃትና ጂሃድን በመቃወም የሚወነጀሉት? እነ አልባኒ፣ ኢብኑ ባዝ፣ ዑሠይሚን፣... አይደሉ እንዴ ለአፍጋኒስታን ጦርነት ሲቀሰቅሱ የነበሩት? እነ ረቢዕ የአፍጋኒስታን ጂሃድ ላይ አልተሳተፉም ወይ?! ህይወታቸው በነዚህ የጥመት አንጃዎች አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ሐቅን በማድረስ ላይ አልተዋደቁምን? እነ ኢሕሳን ኢለሂ ዞሂር በተጠመደ ቦምብ አልተገደሉም? እነ ጀሚሉ ረሕማን ኩነር አፍጋኒስታን ውስጥ አልተገደሉም? እነ ሙቅቢል መስጂድ ውስጥ ከተጠመደ ቦምብ ለትንሽ አልተረፉም? ለህይወታቸው ቢሳሱ ነው’ንዴ ሌሎች የተሸበቡበትን ርእስ ከፍ በማድረግ ደም የጠማቸው የጥፋት አንጃዎችን የሚጋፈጡት? የኢኽዋን ቆሻሾች እንደሚወነጅሏቸው ፈሪዎች ስለሆኑ ነው በዚህ ደረጃ ህይወታቸው አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ወደኋላ የማይሉት? እነዚህ ሳይሞቅ ፈላዎች ጀግና ከሆኑ ለምን ወደ ፍልስጤም አይዘምቱም? ፍልስጤም ብትርቃቸው እዚሁ አፍሪካ ውስጥ ሙስሊሞች የሚበደሉባቸው በርካታ ሃገራት አሉ’ኮ። ፌስቡክ ላይ ከሚፎክሩ ለምን ነፍጥ አንግበው ጫካ አይገቡም? ሁሌ ከዑለማእ ውስጥ ሰለፊዮቹ ላይ፣ ከሃገራት ውስጥ ሳዑዲ ላይ ነው የሚዘምቱት።
ለእስራኤል የደህንነትና የስለላ መረጃዎችን የሚያቀብለው የኩርጂክ የራዳር ማእከል ቱርክ ውስጥ ነው የሚገኘው። ከእስራኤል ከፍተኛ የንግድ አጋሮች ውስጥ አንዷ ቱርክ ነች። ከሙስሊሙ አለም በቱርክ ደረጃ ለሷ ወዳጅ የሆነ የለም። በቅርቡ ቃጠሎ ሲገጥማት የእሳት ማጥፊያ አውሮፕላኖችን የላከች ቱርክ ነች። “የእስራኤል አባት” ተብሎ የሚጠራው ቴዎዶር ሄርዝል ቀብር ላይ የአበባ ጉንጉን ያስቀመጠው ኤርዶጋን ነው። በተለያዩ ጊዜያት የጋራ የጦር ልምምድ ሲያደርጉ እንደነበር የሚታወቅ ነበር። በዚህ ቀውጢ ጊዜ ሳይቀር በጎን ባዶ የቃላት ኳኳታ እያሰሙ ሲያደነዝዙ፣ በሌላ በኩል የንግድ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር ኢኽዋኖችና የነሱን ተውሳክ የተሸከሙ አካላት ነጋ ጠባ “ሳዑዲ፣ ሳዑዲ” እያሉ ማላዘን ነው የሚቀናቸው። ኢላማቸው መሪዎቹ አይደሉም። ወደ ዑለማዎቹ ለመሻገር ነው የነሱን ጉዳይ የሚያነሱት።
እስኪ አሁን “ጂሃድ በደመ–ነፍስ የሚካሄድ ሳይሆን ዝግጅት ይፈልጋል” የሚል ምክር ምን እንከን ይወጣለታል? ሃሳቡን አይቀበሉ! ምናል በቅንነት ተመልክተው ለሌሎች የሚሰጡትን ‘ዑዝር’ ቢሰጧቸው? እንዴትስ እዝነት መቆርቆራቸው በክፋትና በፍርሃት ይተረጎማል? የቢድዐ ልክፍት ያሳበዳቸው ወፈፌዎች ካልሆኑ በስተቀር ይሄ ጤነኛ አእምሮ ላለው የሚሰወር አይደለም። ቤት ውስጥ በሚዘጋጅ የጠርሙስ ቦምብ ነው ኒኩሌር ከታጠቀ ኃይል ጋር የምትዋጋው? በወፍ ማደኛ ወስፈንጠር ነው ከታንክ ጋር የምትፋለመው? በህልም ነው በውን ክላስተር ቦምብ የሚያዘንቡ ጄቶች በወንጭፍ የሚወርዱት? ለመሆኑ ለምንድን ነበር ሙስሊሞች መካ ላይ እያሉ በጂሃድ ያልታዘዙት? ደካማ ስለነበሩ አይደለምን? መዲና ውስጥ አቅማቸው ሲጠነክር’ኮ ነቢዩን ﷺ የተሳደበ አካል እርምጃ ተወስዶበታል። መካ ሳሉስ? ከስድብ በላይ ብዙ አልደረሰባቸውም? የገማ እንግዴ ልጅ አልተጣለባቸውም? ለምን እርምጃ አልወሰዱም? ምክንያት የለውም’ንዴ? ሶሐቦች ያ ሁሉ ሲደርስባቸው፣ እነ ሱመያ እነ ያሲር ሲገደሉ፣ ሌሎች አገር ጥለው እንዲሰደዱ ያደረጋቸው ግፍ ሲያስተናግዱ የፈለገ ይሁን ብለው አሳቻ ቦታ እየጠበቁ ጥቃት ማድረስ አቅቷቸው አልነበረም’ኮ! ቢላል ክፉኛ ሲያንገላታው የነበረውን ኡመያን ለመግደል ከአመታት በኋላ የተካሄደውን የበድር ዘመቻ ሳይጠብቅ ገና ቁስሉ ሳይደርቅ መካ ውስጥ መግደል አቅቶት’ኮ አልነበረም። ሸሪዐው የጂሃድን ትእዛዝ ያዘገየው ያለ ምክንያት ነው’ንዴ? አቅም እንዲያጎለብቱ፣ ዝግጅት እንዲያደርጉ እንጂ! የላቀው አላህ ምንድነው ያለው?
وَأَعِدُّواْ لَهُم مَّا ٱسۡتَطَعۡتُم مِّن قُوَّةٖ وَمِن رِّبَاطِ ٱلۡخَيۡلِ تُرۡهِبُونَ بِهِۦ عَدُوَّ ٱللَّهِ وَعَدُوَّكُمۡ
“ለእነሱም ከማንኛውም ኃይል (መሳሪያ) እና ከታጀቡ ፈረሶችም የቻላችሁትን ሁሉ በእርሱ የአላህን ጠላትና ጠላታችሁን የምታሸብሩበትን አዘጋጁላቸው።" [አልአንፋል፡ 60]
ሶሐቦቹ ይህንን መለኮታዊ ትእዛዝ ተከትለው ጠላትን የሚገዳደር ዝግጅት አድርገዋል። ዛሬ ወደ ጦር ሜዳ የምትጓዘው በፈረስ፣ የምትወረውረውም ቀስት አይደለም። ጠላት አእላፍ ኪሎ ሜትሮችን ርቆ አንተን ማደባየት ይችላል። ሙስሊሙ የትኛው ዝግጅት ነው ያለው? ምናልባት “የሰለጠኑ ፈረሶችን አዘጋጅተናል” ይሉ ይሆን? አይሉም አይባልም እነዚህ ማስተዋል የተሳናቸው ጉዶች? በዓለም ላይ እጅግ አውዳሚ የሆኑ ሃይድሮጂን ቦምቦች፣ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች፣ ግዙፍ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች፣ ጅምላ ጭራሽ ባዮሎጂካል መሳሪያዎች፣ ከራዳር ቁጥጥር ውጭ የሆኑ የተራቀቁ የጦር አውሮፕላኖች፣ ወዘተ የታጠቁት ሙስሊም ሃገራት አይደሉም። ወደ 16 ሺህ ከሚገመተው የዓለም ኒኩሌር 90 ከመቶ በላይ በአሜሪካና በራሺያ እጅ ነው ያለው። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በጃፓን ሂሮሽማና ናጋሳኪ ከተሞች ላይ 2 መቶ ሺህ አካባቢ ህዝብ ያለቀው በሁለት ኒኩሌር ብቻ ነው። ይህን ያክል ርቀዋል። የዛሬ ሙስሊም ሃገራት የ1945ቷን ጃፓን አያክሉም። ከመሆኑም ጋር ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ ተንኮታኩታ ነበር እጅ የሰጠችው። ጋዳፊን በቀናት ውስጥ ያሽመደመደው የፈረንሳይ አየር ኃይል እንጂ ተቃዋሚዎቹማ እዚህ ግባ የሚባል አቅም አልነበራቸውም። በርካቶች ዘንድ ተጋኖ ተስሎ የነበረው የሳዳም ጦር እንደ ቅቤ የቀለጠው ያለ ምክንያት አይደለም!! “የዐረብ ሃገራት ናቸው ጉድ የሰሩት” እያሉ ዋናውን ምስል መዘንጋት እራስን ማታለል ነው? ወደድንም ጠላንም በመሃላችን ያለው ርቀት ከምንገምተው በላይ እጅግ የሰፋ ነው። 
እጅግ በርካታ “ሙፈኪሮች” ያለንበትን ተጨባጭ በውል አልተረዱም። ምነው ችግሩ በዚህ በቅቶ መከራችን በቀለለ?! በዚህ ሰመመናቸው ውስጥ ሆነው “ፊቅሁል ዋቂዕ አልገባቸውም” እያሉ ዑለማዎች ላይ መዝመታቸው ባሰ እንጂ። የነሱ የጥመት አውራዎች ሲነኩ ግን “ዑለማእ ተሰደበ” እያሉ አገር ያቃጥላሉ። ዑለማዎቻችንን ተውልን። ክፍተት ቢኖራቸው እንኳ እንደ ቀርዷዊ ካሉ የጥፋት ቁንጮዎች ጋር የሚነፃፀሩ አይደሉም። በምን ስሌት ነው እነዚያ እየታለፉ በነዚህ ላይ ሌት ከቀን የሚዘመተው?!
እንዲህ አይነቱ ኸዋሪጅ ጋር እየዋለ፣ የኸዋሪጅ ፊክራ እየጠጣ፣ ኸዋሪጅኛ የሚያስነጥስ የጥጃ ቀንዳም ነገሮችን በውል መመዘን፣ ግራ ቀኝ መመልከት የሚባል አያውቅም። ሙስሊሙ ዓለም ከአሜሪካም፣ ከራሺያም፣ ከፈረንሳይም፣ ከእንግሊዝም፣ ከቻይናም፣ ከህንድም፣ ከእስራኤልም ጋር እንዲዋጋ ነው የሚሹት። ተጨባጩ ግን እንኳን ከነዚህ ሁሉ ቀርቶ አንዱንም በሚቋቋምበት ቁመና ላይ አለመሆኑ ነው። ቱርክ ጦሯን ድንበር ተሻግራ ሶሪያ ውስጥ ብታስገባም "ለሃገሬ ስጋት ናቸው" የምትላቸውን የኩርድ ታጣቂዎች ከማጥቃት ባለፈ በሻረል አሰድን ለመንካት የማትደፍረው ወዳው አይደለም፤ ራሺያን ፈርታ እንጂ። ቻይና “የግዛቴ አካል ናት” የምትላትን


>>Click here to continue<<

ፉርቃን ኦንላይን ቁርኣን ማዕከል




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)