TG Telegram Group & Channel
እንደ.....ገጣሚ | United States America (US)
Create: Update:

አንቺን እንደማርያም ማርያምን እንዳንቺ!!
ኑዛዜ!

ስለ ማርያም!...
በዘመነ ኦሪት
በዘመነ መንሱት
ባረጀ ያንጊዜ
ባፈጀ አባዜ
በጥንት ተክዤ...
እልፍ ሴት ደናግል!
እልፍ የውበት ሰብል!
በሞላበት አለም
ማን አለ እሷን ያክል?
እላለሁ!...
***
ስለአንቺ!...
በዘመነ ኪዳን
በዘመነ አዲስ
በዘመነ መንዲስ
ዘመነ ሁካታ
ዘመነ ጫጫታ
ወጣት ተሰፍ ይዤ
በመፃኢ አባዜ
ከአሁን ተሰፍቼ
እልፍ ቆንጆ መሃል
እልፍ እንስት ሸኝቼ
እልፍ እንስት ስቀበል
አሰስ ገሠሠስ ግርዱ
በሞላበት አለም
ማን አለ እሷን ያክል!?
እላለሁ!...

ማርያም!...
ቅዱስም ንጉስም
ፈጣሪም አምላክም
ሁሉን ቻይ ልጅ ያላት
እናት ስትሆን ባርያ... ገረድ ስትሆን እናት!

አንቺ!...
እርኩስም ጭሠኛም
ተፈጣሪም ሎሌ
ደካማ ጠንካራ መጠሪያ ልጅ የለሽ
እናትም አገልጋይ ልቶኝ ያልተጠራሽ!

ማርያምን!...
እቴ ሙሽራዬ ይላታል ጠቢቡ
ከህሊናው ሸራ
ከነፍሱ ብራና
ውበት መልኳን ነድፎ
ኪዳነ ቋሏ ላይ ነብስያውን ፅፎ።
የአብራሀም እናት
የይሳቅ እመቤት
ያያእቆብ ተስፍ
የዬሴፍ መለከት።
የዳዊት ዝማሬ
የሰለሞን ቅኔ
የእሳያስ ልሳን
የህዝቅኤል ወኔ
የኦሪት ናፍቆት ታቦት
የአዲስ ኪዳን መክሊት።
ይላሉ...

አንቺን!
ዘመናይ ማርዬ
ይልሻል መንፈሴ
ፈገግታና ሳቅሽ
ተጣብቶ ከነፍሴ
ምን ጠቢብ ባትሆንም
ያይኗ ሉል
መኳኳል
የአዳም መሠናክል
የባቷ አወራድ
ከሀጢያት የሚማግድ።
ይላሉ!...

ማር ይሏት መድሃኒት
ያም ምትባል ፈውስ
የመለኮት መባ
ንፅህት ህያው ቅዱስ።
ይሏታል!...

ሬት ይሏት ምሬት
ጭራ ቀረሽ ደዌ
የጋኔል መስፈሪያ
ርኩስ...ርጉም... ክፍ የጥፍት ህላዌ
ይሉሻል!...

ቅዱስም ንጉስም
ፈጣሪም አምላክም
ኤልሻዳይ ልጅ ያላት
እናት ስትሆን ባርያ... ገረድ ስትሆን እናት።
ይሏታል!...

እርኩስም ጭሠኛም
ተፈጣሪም ሎሌ
ደካማ ጠንካራ መጠሪያ ልጅ የለሽ
እናትም አገልጋይ ልቶኝ '"ያልተጠራሽ።
ይሉሻል!...

እናልሽ!.....
አንቺን እንደማርያም ማርያምን እንዳንቺ!! ቢረግልኝ ዘመን ቢራራልኝ ጊዜ
ያበቃ ይሆናል ይህ ሁሉ ኑዛዜ።

ጥቅምት 21/2015 ሞጆ

አንቺን እንደማርያም ማርያምን እንዳንቺ!!
ኑዛዜ!

ስለ ማርያም!...
በዘመነ ኦሪት
በዘመነ መንሱት
ባረጀ ያንጊዜ
ባፈጀ አባዜ
በጥንት ተክዤ...
እልፍ ሴት ደናግል!
እልፍ የውበት ሰብል!
በሞላበት አለም
ማን አለ እሷን ያክል?
እላለሁ!...
***
ስለአንቺ!...
በዘመነ ኪዳን
በዘመነ አዲስ
በዘመነ መንዲስ
ዘመነ ሁካታ
ዘመነ ጫጫታ
ወጣት ተሰፍ ይዤ
በመፃኢ አባዜ
ከአሁን ተሰፍቼ
እልፍ ቆንጆ መሃል
እልፍ እንስት ሸኝቼ
እልፍ እንስት ስቀበል
አሰስ ገሠሠስ ግርዱ
በሞላበት አለም
ማን አለ እሷን ያክል!?
እላለሁ!...

ማርያም!...
ቅዱስም ንጉስም
ፈጣሪም አምላክም
ሁሉን ቻይ ልጅ ያላት
እናት ስትሆን ባርያ... ገረድ ስትሆን እናት!

አንቺ!...
እርኩስም ጭሠኛም
ተፈጣሪም ሎሌ
ደካማ ጠንካራ መጠሪያ ልጅ የለሽ
እናትም አገልጋይ ልቶኝ ያልተጠራሽ!

ማርያምን!...
እቴ ሙሽራዬ ይላታል ጠቢቡ
ከህሊናው ሸራ
ከነፍሱ ብራና
ውበት መልኳን ነድፎ
ኪዳነ ቋሏ ላይ ነብስያውን ፅፎ።
የአብራሀም እናት
የይሳቅ እመቤት
ያያእቆብ ተስፍ
የዬሴፍ መለከት።
የዳዊት ዝማሬ
የሰለሞን ቅኔ
የእሳያስ ልሳን
የህዝቅኤል ወኔ
የኦሪት ናፍቆት ታቦት
የአዲስ ኪዳን መክሊት።
ይላሉ...

አንቺን!
ዘመናይ ማርዬ
ይልሻል መንፈሴ
ፈገግታና ሳቅሽ
ተጣብቶ ከነፍሴ
ምን ጠቢብ ባትሆንም
ያይኗ ሉል
መኳኳል
የአዳም መሠናክል
የባቷ አወራድ
ከሀጢያት የሚማግድ።
ይላሉ!...

ማር ይሏት መድሃኒት
ያም ምትባል ፈውስ
የመለኮት መባ
ንፅህት ህያው ቅዱስ።
ይሏታል!...

ሬት ይሏት ምሬት
ጭራ ቀረሽ ደዌ
የጋኔል መስፈሪያ
ርኩስ...ርጉም... ክፍ የጥፍት ህላዌ
ይሉሻል!...

ቅዱስም ንጉስም
ፈጣሪም አምላክም
ኤልሻዳይ ልጅ ያላት
እናት ስትሆን ባርያ... ገረድ ስትሆን እናት።
ይሏታል!...

እርኩስም ጭሠኛም
ተፈጣሪም ሎሌ
ደካማ ጠንካራ መጠሪያ ልጅ የለሽ
እናትም አገልጋይ ልቶኝ '"ያልተጠራሽ።
ይሉሻል!...

እናልሽ!.....
አንቺን እንደማርያም ማርያምን እንዳንቺ!! ቢረግልኝ ዘመን ቢራራልኝ ጊዜ
ያበቃ ይሆናል ይህ ሁሉ ኑዛዜ።

ጥቅምት 21/2015 ሞጆ


>>Click here to continue<<

እንደ.....ገጣሚ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)