TG Telegram Group & Channel
Ahadu picture | United States America (US)
Create: Update:

‍ 😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

💞ክፍል 4

✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ
.
.
.
ዮርዳኖስ ቤት ሲገባ ደነገጠ አፉን ከፍቶ ቀረ።ቤቱ በዲም ላይት አሸብርቋል ።ከበሩ ፊት ለፊት የ ዮርዳኖስ እና የሔዋን ፎቶ በትልቅ መስታወት ተንጠልጥሏል።ከላይ እንኳን ለሁለተኛ አመት የፍቅር ጅማሪያችሁ አደረሳችሁ።የሚል ወረቀት ተለጥፏል።ልቡ ተሸበረ።"ዛሬ የሚፈጠር ነገር አለ እንጂ ካለነገር ልቤ አልፈራም፤ሔዋንም ልክ አልነበረችም"አለ በውስጡ ።እህቱ ቤዛ ወደ ሳሎን ገባች እና "ሰርፕራይዝ"ብላ ከሃሳቡ አባነነችው።
"በቃ ስራ አጥ መሆን እንደዚህ ነው የሚያደርገው? ለአንቺ ስራ ፈጠራ መሆኑ ነው አይደል?እስኪ ይሔን ሁሉ ለደከምሽበት ምንያህል ክፍያ ነው የምትጠይቂኝ?"አለ ዮርዲ ለመቀለድ
ቤዛ አኮረፈች እና ተመልሳ ወደ እናቷ ሔደች ።
"አንተ ምላሳም ሰምቼሃለሁ!አንተን ለማስደሰት ይሔንን ሁሉ ደክማ እንደዚህ ነው መልስህ?"አለች ወይዘሮ አለም እየሳቀች ።
እውነት ነው ቤዛዊት ከተመረቀች ድፍን ሁለት አመት ሞላት።ስራ የሚባል ነገር የለም።ከአባቷ ከአቶ ተሾመ ጋር ንግዱን እያጦጧፈችው ነው።አሁንማ ተስፋ ቆርጣ የስራ ማስታወቂያ ማየት ካቆመች ስድስት ወር ሞላት አረ አንዲያውም የተመረቀችበትን የትምህረት መስክ ሁሉ ሳትረሳው አልቀረችም ።
ዮርዲ ጓዳ ሲገባ እናቱ ምግብ በመስራት ተጠምዳለች።ቤዛ ደግሞ ለምቦጯን ጥላ ተቀምጣለች።
"አንቺ ደግሞ ሰው መቀለድ አይችልም እንዴ?"አለ ዮርዲ ፀጉሯን እንደ ህፃን ልጅ እዬደባበሰ
"አንደኛ ስራ አጥ አትበለኝ፤ሲቀጥል እኔ ስራ አጥ አይደለሁም ነጋዴ ነኝ አሺ።"አለች ኮስተር ብላ።
"እስኪ በእኔ ሞት በስነፅሁፍ ተመርቆ ነጋዴ አይከብድም " አለት ዮርዲ።
"አሱን ከጥቂት አመታት በኋላ በእኔ ቦታ ስትሆን ትነግረኛለህ ወሬኛ"አለች ቤዛ
"አንተ ስራ ፈት ሒድ ወደ ክፍልህ አባትህ እቃ አስቀምጦልሀል"አለች ወይዘሮ አለም
"እእእ ስራ ፈት ብለውማ የሰው ሞራል አይንኩ ወይዘሮ አለም"አለና ጓዳውን ለቆ እየወጣ ዞር ብሎ ቤዛን አየት ሲያደርጋት ነጠላ ጫማዋን አውልቃ ጀርባውን አቀመሰችው።ሳሎኑን አቋርጦ ወደ ክፍሉ እየሮጠ ገባ።
"ደግ አደረግሽ ትንሽ ምላሱን አርፈን እንቆያለን"አለች እና ወይዘሮ አለም ተሳሳቁ።
ዮርዳኖስ ክፍሉ ሲገባ አልጋው ላይ አዲስ ልብስ ተቀምጦለታል።ዋው አለና አንስቶ ተመለከተው።ሰማያዊ ጅንስ ሱሪ እና ብሉ ብላክ አጀ ጉርድ ሸሚዝ።የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ እና አዲሱን ሸሚዝ ለበሰው ።ወደ መስታወቱ ተጠገና ራሱን እየተመለከተ ቁልፎችን ቆለፋቸው።
"አንተ ያበደ ነው ሸበላ ነው የሆንከው
"አለች እልፍነሽ በመስኮት ታይ ኖሯል ልብስ እያጠበች ።
"አረ ተይ አልፊቱ አታሹፊብኝ" አለ ዮርዳኖስ
"አባቴ ይሙት ጋሼ ምርጫ ይችላሉ"አለች እልፍነሽ
"አንቺ ግን እስከ አሁን አጥበሽ አትጨርሽም እንዴ? የዛሬው ደግሞ ከአስራ ሁለት እስከ አስራሁለት ሰዐት ነው እንዴ አጠባው"አለ ዮርዲ
"ምን ባክህ ኬኩን ላዝዝ ሔጄ ነበር ለዛ ነው"አለችው
"የምን ኬክ ነው ቆይ እናንተ ሰዎች እንዴ ዛሬ ምን የተለየ ነገር አለ።እኔና እሷ እኮ የምናከብረው እዛው ከምንገናኝበት የሾላ ዋርካ ላይ ነው።"አለ ተገርሞ
"በል ስራ አስፈታኸኝ" ብላ ወደ ልብስ አጠባዋ ገባች።እሱም መዘነጡን ተያያዘው ።አባቱ የገዛለትን ሱሪ ለበሰው እና አጁን ወደ ኪሱ ሲከተው ኪሱ ውስጥ የሆነ ነገር አገኘ።በፍጥነት አወጣው እና ሲመለከተው ትንሽ ካርቶን ነች።ከፈተው።ውስጡ ሀብል ነበር ።ከካርቶኗ አወጣ እና ሲያይ ተንጠልጣዩ ጋር ኤች H ፊደል አለ።እንዴ "አባዬ ስሜ ጠፋበት እንዴ?" አለና አንገቱ ላይ አንጠልጥለው።ዝንጥ ብሎ ከክፍሉ ወጣ እና ወደ ጓዳ ተመለሰ።
"ትፍ ትፍ ከአይን ያውጣህ ልጄ! አንተ 18ኛ አመትህን እንኳን ስታከብር እንደዚህ አልዘነጥክም።"አለች እና እናቱ ግንባሩን ሳም አደረገችው
"ዛሬ ምሳ ሰዓት የለንም እንዴ 9ኝ ሰዐት አየሆነ እኮ ነው"
"ምነው ራበህ እንዴ" አለች ወይዘሮ አለም
"አይ እንደሱ እንኳን አይደለም ግን አባዬም የለም ብዬ ነው"አለ
"አባትህ እስኪመጣ እኔም እጨርሳለሁ ሒድ ለደሳለኝ ደውልለት የእሱም እቃ ተቀምጦለታል ቤዛ ክፍል አለልህ"አለች ወይዘሮ አለም ።
ዮርዳኖስ ግራ ተጋባ "ቆይ እነዚህ ሰወች ምን አስበው ነው?" ይሔ ሁሉ ሽር ጉድ ምንድን ነው።እናቱ ብዙ የድስት አይነት ደርድራለች ።ማህበር ያለ ነው ያስመሰለችው ።እንዲህ እንደተወዛገበ ወደ ሳሎን ሔደና ለደሳለኝ ደውሎ አሁን እንዲመጣ ነግሮት ወደ ቤዛ ክፍል ሔደና ለደሳለኝ የተቀመጠለትን እቃ አየው። ገረመው የእሱን አይነት ልብስ ነበር የቀመጠው ።ወደ ክፍሉ ይዞት ሔዶ ተቀመጠ።የ ዮርዳኖስ አባት የሁለቱን ጓደኛሞች ፍቅር ሲያወራ ውሎ ቢያድር አይጠግብም።በሁለቱ ልጆች ምክንያት ቤተሰቦቻቸው ተዛምደዋል። በእድሜ ደሳለኝ አመት ይበልጣል። ደሳለኝ ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ በሶፍትዌር አንድ አመት አስቆጥሮ ነው የመጣው።ዮርዲ ደግሞ ዩኒቨርስቲ ለመግባት ውጤት እየጠበቀ ነው።
ቀና አለና ከግድግዳው ጋር የተሰቀለውን የሔዋንን ፎቶ ተመለከተ ።"የእኔ ልዕልት ሺ አመት ኑሪልኝ"አለ ፎቶዋ ላይ እንዳፈጠጠ።
ሔዋን ቀይ መልክ ያላት፣አፍንጫዋ ሰልከክ ብሎ የወረደ፣ጥርሶቿ በስርዓት የተቸመቸሙ እና ብርሀን የሚፈነጥቁት አይኖቿ ዛጎል የሚያካክሉ ሲሆኑ ፀጉሯ ከጀርባዋ ላይ ወርዶ ወርዶ እንደቄጠማ የተነሰነሰ ጡቶቿ የአራት መከራክር ተራራን መስለው የተቀሰሩ።አጠር ያለ ቁመና ያላት እና እና ቀጠን ያለች ሰትሆን ወገቧ ችቦ አይሞላም ወገቧ ተብሎ የተዘፈነላት አይነት ሴት።በአጠቃላይ ውብ የሆነች እንስት ነች።
"አንተ እስከ አሁን አበባውን አልገዛኸውም "አለና ደሳለኝ ዮርዳኖስን ከሀሳቡ አባነነው።


ይቀጥላል

@Ethio_leboled #Share
❥❥________⚘_______❥❥

‍ 😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

💞ክፍል 4

✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ
.
.
.
ዮርዳኖስ ቤት ሲገባ ደነገጠ አፉን ከፍቶ ቀረ።ቤቱ በዲም ላይት አሸብርቋል ።ከበሩ ፊት ለፊት የ ዮርዳኖስ እና የሔዋን ፎቶ በትልቅ መስታወት ተንጠልጥሏል።ከላይ እንኳን ለሁለተኛ አመት የፍቅር ጅማሪያችሁ አደረሳችሁ።የሚል ወረቀት ተለጥፏል።ልቡ ተሸበረ።"ዛሬ የሚፈጠር ነገር አለ እንጂ ካለነገር ልቤ አልፈራም፤ሔዋንም ልክ አልነበረችም"አለ በውስጡ ።እህቱ ቤዛ ወደ ሳሎን ገባች እና "ሰርፕራይዝ"ብላ ከሃሳቡ አባነነችው።
"በቃ ስራ አጥ መሆን እንደዚህ ነው የሚያደርገው? ለአንቺ ስራ ፈጠራ መሆኑ ነው አይደል?እስኪ ይሔን ሁሉ ለደከምሽበት ምንያህል ክፍያ ነው የምትጠይቂኝ?"አለ ዮርዲ ለመቀለድ
ቤዛ አኮረፈች እና ተመልሳ ወደ እናቷ ሔደች ።
"አንተ ምላሳም ሰምቼሃለሁ!አንተን ለማስደሰት ይሔንን ሁሉ ደክማ እንደዚህ ነው መልስህ?"አለች ወይዘሮ አለም እየሳቀች ።
እውነት ነው ቤዛዊት ከተመረቀች ድፍን ሁለት አመት ሞላት።ስራ የሚባል ነገር የለም።ከአባቷ ከአቶ ተሾመ ጋር ንግዱን እያጦጧፈችው ነው።አሁንማ ተስፋ ቆርጣ የስራ ማስታወቂያ ማየት ካቆመች ስድስት ወር ሞላት አረ አንዲያውም የተመረቀችበትን የትምህረት መስክ ሁሉ ሳትረሳው አልቀረችም ።
ዮርዲ ጓዳ ሲገባ እናቱ ምግብ በመስራት ተጠምዳለች።ቤዛ ደግሞ ለምቦጯን ጥላ ተቀምጣለች።
"አንቺ ደግሞ ሰው መቀለድ አይችልም እንዴ?"አለ ዮርዲ ፀጉሯን እንደ ህፃን ልጅ እዬደባበሰ
"አንደኛ ስራ አጥ አትበለኝ፤ሲቀጥል እኔ ስራ አጥ አይደለሁም ነጋዴ ነኝ አሺ።"አለች ኮስተር ብላ።
"እስኪ በእኔ ሞት በስነፅሁፍ ተመርቆ ነጋዴ አይከብድም " አለት ዮርዲ።
"አሱን ከጥቂት አመታት በኋላ በእኔ ቦታ ስትሆን ትነግረኛለህ ወሬኛ"አለች ቤዛ
"አንተ ስራ ፈት ሒድ ወደ ክፍልህ አባትህ እቃ አስቀምጦልሀል"አለች ወይዘሮ አለም
"እእእ ስራ ፈት ብለውማ የሰው ሞራል አይንኩ ወይዘሮ አለም"አለና ጓዳውን ለቆ እየወጣ ዞር ብሎ ቤዛን አየት ሲያደርጋት ነጠላ ጫማዋን አውልቃ ጀርባውን አቀመሰችው።ሳሎኑን አቋርጦ ወደ ክፍሉ እየሮጠ ገባ።
"ደግ አደረግሽ ትንሽ ምላሱን አርፈን እንቆያለን"አለች እና ወይዘሮ አለም ተሳሳቁ።
ዮርዳኖስ ክፍሉ ሲገባ አልጋው ላይ አዲስ ልብስ ተቀምጦለታል።ዋው አለና አንስቶ ተመለከተው።ሰማያዊ ጅንስ ሱሪ እና ብሉ ብላክ አጀ ጉርድ ሸሚዝ።የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ እና አዲሱን ሸሚዝ ለበሰው ።ወደ መስታወቱ ተጠገና ራሱን እየተመለከተ ቁልፎችን ቆለፋቸው።
"አንተ ያበደ ነው ሸበላ ነው የሆንከው
"አለች እልፍነሽ በመስኮት ታይ ኖሯል ልብስ እያጠበች ።
"አረ ተይ አልፊቱ አታሹፊብኝ" አለ ዮርዳኖስ
"አባቴ ይሙት ጋሼ ምርጫ ይችላሉ"አለች እልፍነሽ
"አንቺ ግን እስከ አሁን አጥበሽ አትጨርሽም እንዴ? የዛሬው ደግሞ ከአስራ ሁለት እስከ አስራሁለት ሰዐት ነው እንዴ አጠባው"አለ ዮርዲ
"ምን ባክህ ኬኩን ላዝዝ ሔጄ ነበር ለዛ ነው"አለችው
"የምን ኬክ ነው ቆይ እናንተ ሰዎች እንዴ ዛሬ ምን የተለየ ነገር አለ።እኔና እሷ እኮ የምናከብረው እዛው ከምንገናኝበት የሾላ ዋርካ ላይ ነው።"አለ ተገርሞ
"በል ስራ አስፈታኸኝ" ብላ ወደ ልብስ አጠባዋ ገባች።እሱም መዘነጡን ተያያዘው ።አባቱ የገዛለትን ሱሪ ለበሰው እና አጁን ወደ ኪሱ ሲከተው ኪሱ ውስጥ የሆነ ነገር አገኘ።በፍጥነት አወጣው እና ሲመለከተው ትንሽ ካርቶን ነች።ከፈተው።ውስጡ ሀብል ነበር ።ከካርቶኗ አወጣ እና ሲያይ ተንጠልጣዩ ጋር ኤች H ፊደል አለ።እንዴ "አባዬ ስሜ ጠፋበት እንዴ?" አለና አንገቱ ላይ አንጠልጥለው።ዝንጥ ብሎ ከክፍሉ ወጣ እና ወደ ጓዳ ተመለሰ።
"ትፍ ትፍ ከአይን ያውጣህ ልጄ! አንተ 18ኛ አመትህን እንኳን ስታከብር እንደዚህ አልዘነጥክም።"አለች እና እናቱ ግንባሩን ሳም አደረገችው
"ዛሬ ምሳ ሰዓት የለንም እንዴ 9ኝ ሰዐት አየሆነ እኮ ነው"
"ምነው ራበህ እንዴ" አለች ወይዘሮ አለም
"አይ እንደሱ እንኳን አይደለም ግን አባዬም የለም ብዬ ነው"አለ
"አባትህ እስኪመጣ እኔም እጨርሳለሁ ሒድ ለደሳለኝ ደውልለት የእሱም እቃ ተቀምጦለታል ቤዛ ክፍል አለልህ"አለች ወይዘሮ አለም ።
ዮርዳኖስ ግራ ተጋባ "ቆይ እነዚህ ሰወች ምን አስበው ነው?" ይሔ ሁሉ ሽር ጉድ ምንድን ነው።እናቱ ብዙ የድስት አይነት ደርድራለች ።ማህበር ያለ ነው ያስመሰለችው ።እንዲህ እንደተወዛገበ ወደ ሳሎን ሔደና ለደሳለኝ ደውሎ አሁን እንዲመጣ ነግሮት ወደ ቤዛ ክፍል ሔደና ለደሳለኝ የተቀመጠለትን እቃ አየው። ገረመው የእሱን አይነት ልብስ ነበር የቀመጠው ።ወደ ክፍሉ ይዞት ሔዶ ተቀመጠ።የ ዮርዳኖስ አባት የሁለቱን ጓደኛሞች ፍቅር ሲያወራ ውሎ ቢያድር አይጠግብም።በሁለቱ ልጆች ምክንያት ቤተሰቦቻቸው ተዛምደዋል። በእድሜ ደሳለኝ አመት ይበልጣል። ደሳለኝ ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ በሶፍትዌር አንድ አመት አስቆጥሮ ነው የመጣው።ዮርዲ ደግሞ ዩኒቨርስቲ ለመግባት ውጤት እየጠበቀ ነው።
ቀና አለና ከግድግዳው ጋር የተሰቀለውን የሔዋንን ፎቶ ተመለከተ ።"የእኔ ልዕልት ሺ አመት ኑሪልኝ"አለ ፎቶዋ ላይ እንዳፈጠጠ።
ሔዋን ቀይ መልክ ያላት፣አፍንጫዋ ሰልከክ ብሎ የወረደ፣ጥርሶቿ በስርዓት የተቸመቸሙ እና ብርሀን የሚፈነጥቁት አይኖቿ ዛጎል የሚያካክሉ ሲሆኑ ፀጉሯ ከጀርባዋ ላይ ወርዶ ወርዶ እንደቄጠማ የተነሰነሰ ጡቶቿ የአራት መከራክር ተራራን መስለው የተቀሰሩ።አጠር ያለ ቁመና ያላት እና እና ቀጠን ያለች ሰትሆን ወገቧ ችቦ አይሞላም ወገቧ ተብሎ የተዘፈነላት አይነት ሴት።በአጠቃላይ ውብ የሆነች እንስት ነች።
"አንተ እስከ አሁን አበባውን አልገዛኸውም "አለና ደሳለኝ ዮርዳኖስን ከሀሳቡ አባነነው።


ይቀጥላል

@Ethio_leboled #Share
❥❥________⚘_______❥❥


>>Click here to continue<<

Ahadu picture




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)


Warning: Undefined array key 3 in /var/www/hottg/function.php on line 115

Fatal error: Uncaught mysqli_sql_exception: Connection refused in /var/www/db.php:8 Stack trace: #0 /var/www/db.php(8): mysqli_connect() #1 /var/www/hottg/function.php(212): db() #2 /var/www/hottg/function.php(115): select() #3 /var/www/hottg/post.php(343): daCache() #4 /var/www/hottg/route.php(63): include_once('...') #5 {main} thrown in /var/www/db.php on line 8