TG Telegram Group & Channel
Ahadu picture | United States America (US)
Create: Update:

ሽ የሚነሳ ነገር አይደለም"አለምየ ይቅርታ አድርጊልኝ" አለ ከጉልበቷ ሳይነሳ።ከአባ ውጭ ሌላው ሰው በሙሉ ግራ ተጋብቷል
አባም በግንባራቸው ለወይዘሮ አለም ተግሳፅ ሰጡ።
"እንዴ ምን በደልከኝ እና ይቅርታ ትጠይቀኛለህ"አለች
"ይቅርታ አድርጌልሃለሁ ካላልሽ በፍፁም አልነሳም"አለ
"አሺ ይቅርታ አድርጌልሃለሁ"አለች ግራ ተጋብታ
አባም አቶ ተሾመን ወክለው በምክር እያዋዙ በተግሳፅ እያለዘቡ መጨረሻ ላይ እውነታውን ዘረገፉት።ለአመታት ተደብቆ የኖረ ጎረምሳ ወንድ ልጅ እንዳለው ተናገሩ።ወይዘሮ አለም መብረቅ የወረደባት ያክል በድንጋጤ ድርቅ ብላ ቀረች።ቤዛም ደንግጣለች።ዮርዳኖስ ደንግጧል ግን ደግሞ ወንድም እንዳለው ሲሰማ ደስ ብሎታልም።እልፍነሽ በመገረም ጭንቅላቷን ትነቀንቀዋለች።
ወይዘሮ አለም የስሜት ህዋሳቶቿ እየተነቃቁ ሲመጡ ትቀውጠው ጀመር።"ተሾመ አንተ በእኔ ላይ ሔድክ በእኔ ላይ ሌላ ሴት ተኛህ።"እያለች ሳሎኑን ትንጎራደድበት ይዛለች ።
አባም ተቆጥተው አስቀመጧት እና"ተይ ልጄ አስቦበት አይደለም አባትሽ ድህነትነቱን ነግረው ከእነ ልጁ ነጥቀው ሲወስዱበት ብቸኝነቱን አልችለው ብሎ በመጠጥ ሀይል ወደቀ።ልጄ ተይ እንደዚህ አትሁኝ"አሉ ተቆጥተው ።
ወይዘሮ አለም ተለያይተው በነበረበት ሰዐት መሆኑን እና እሷ እያለች ሔዶ አለመሆኑን ስትሰማ ትንሽ ሆዷ ውስጥ ሲነድ የነበረው እሳት መጥፋት ጀመረ።
"አባም ይቅር ሰንል ነው ይቅር የምንባለው እያሉ" ሲመክሯት አምሽተው አረጋግተዋት አቶ ተሾመን ከልቧ ይቅርታውን እንድትቀበል አድርገው ነገ ልጅ እና እናት መጥተው እንደሚተዋወቁ ተናግረው ሔዶ።
ወይዘሮ አለም ከሁሉም ሰው ቀድማ ገብታ ተኛች።ዮርዲ ደግሞ ወንድሙን ለማወቅ ጓጉቶ ሲያስብ አመሼ።ቤዛም ምን አለበት ሴት በሆነች ማለቷ አልቀረም ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እሁድ ከሰዐት በኋላ ......................................
ቃለአብ ዝንጥ ብሏል የሚለው ቃል አይገልፀውም።አረ እማዬ ምንድን ነው ምስራቹን ንገሪኝ አለ።
"ወይ አንተ ደግሞ፤በቃ እሺ አባትና እህት ወንድምህን ልትተዋወቅ ነው"ብላ አበሰረችው
"ቃለአብ በደስታ ዘሎ እናቱ ላይ ተጠመጠመባት።ጉንጯን እያገላበጠ በደስታ ሳማት።
ከሁሉም በላይ ወንድሙን ለማወቅ ቋመጠ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እነ ወይዘሮ አለም ቤቱን ሞቅ ደመቅ አድርገው ምግቡን በእየፈርጁ ሰርተው እንግዶቹን እየጠበቁ ነው።ዮርዲም እንደ ቤተሰብ አባል የሚቆጠረውን ደሴን እውነቱን ነግሮት ከዮርዲ ጋር እሚሆነውን እየጠበቁ ነው።
በር ተንኳኳ ሁሉም ከመቀመጫቸው ተነሱ።እልፍነሽ በሩን ከፈተች።እናት እና ልጅ ገቡ ።ሳሎን በር ላይ እንደደረሱ ቃለአብ ከዮርዳኖስ እና ከደሴ ጋር አይን ለአይን ተጋጨ።ዮርዲ ድንገት ልቡ ቀጥ ስትል ተሰማው።በህይወት ዘመኑ እንኳን ይሔንን ያክል የደነገጠበትን ቀን አያስታውስም።ቃለአብም ልቡ ከዳችው ደነገጠ ልቡን በእጁ ያዘ።ደሴ የዮርዳኖስን ህልም እና ወንድማማችነት እያያያዘ አግራሞት ተሞልቷል።
ዮርዳኖስ ሮጦ ቃለአብ ወንድሜ አለ ቃለአብም ዮርዲዬ አለ ተቃቀፋ።ህልም አይደለም አይደል ቃል አለ ዮርዲ ።አንተን ልጠይቅህ ወንድሜ እየቃዠሁ አይደለም አለ ጥያቄውን በጥያቄ እየደገመ።
ሙሉ ቤተሰቡ ተዋወቀ።ቃለአብ ተሾመ እና ዮርዳኖስ ተሾመ ከሁለት ማህፀን ግን በአንድ ቀን የተወለዱ የሁለት ማህፀን መንትዮች።

ይቀጥላል

@Ethio_leboled #Share
❥❥________⚘_______❥❥

ሽ የሚነሳ ነገር አይደለም"አለምየ ይቅርታ አድርጊልኝ" አለ ከጉልበቷ ሳይነሳ።ከአባ ውጭ ሌላው ሰው በሙሉ ግራ ተጋብቷል
አባም በግንባራቸው ለወይዘሮ አለም ተግሳፅ ሰጡ።
"እንዴ ምን በደልከኝ እና ይቅርታ ትጠይቀኛለህ"አለች
"ይቅርታ አድርጌልሃለሁ ካላልሽ በፍፁም አልነሳም"አለ
"አሺ ይቅርታ አድርጌልሃለሁ"አለች ግራ ተጋብታ
አባም አቶ ተሾመን ወክለው በምክር እያዋዙ በተግሳፅ እያለዘቡ መጨረሻ ላይ እውነታውን ዘረገፉት።ለአመታት ተደብቆ የኖረ ጎረምሳ ወንድ ልጅ እንዳለው ተናገሩ።ወይዘሮ አለም መብረቅ የወረደባት ያክል በድንጋጤ ድርቅ ብላ ቀረች።ቤዛም ደንግጣለች።ዮርዳኖስ ደንግጧል ግን ደግሞ ወንድም እንዳለው ሲሰማ ደስ ብሎታልም።እልፍነሽ በመገረም ጭንቅላቷን ትነቀንቀዋለች።
ወይዘሮ አለም የስሜት ህዋሳቶቿ እየተነቃቁ ሲመጡ ትቀውጠው ጀመር።"ተሾመ አንተ በእኔ ላይ ሔድክ በእኔ ላይ ሌላ ሴት ተኛህ።"እያለች ሳሎኑን ትንጎራደድበት ይዛለች ።
አባም ተቆጥተው አስቀመጧት እና"ተይ ልጄ አስቦበት አይደለም አባትሽ ድህነትነቱን ነግረው ከእነ ልጁ ነጥቀው ሲወስዱበት ብቸኝነቱን አልችለው ብሎ በመጠጥ ሀይል ወደቀ።ልጄ ተይ እንደዚህ አትሁኝ"አሉ ተቆጥተው ።
ወይዘሮ አለም ተለያይተው በነበረበት ሰዐት መሆኑን እና እሷ እያለች ሔዶ አለመሆኑን ስትሰማ ትንሽ ሆዷ ውስጥ ሲነድ የነበረው እሳት መጥፋት ጀመረ።
"አባም ይቅር ሰንል ነው ይቅር የምንባለው እያሉ" ሲመክሯት አምሽተው አረጋግተዋት አቶ ተሾመን ከልቧ ይቅርታውን እንድትቀበል አድርገው ነገ ልጅ እና እናት መጥተው እንደሚተዋወቁ ተናግረው ሔዶ።
ወይዘሮ አለም ከሁሉም ሰው ቀድማ ገብታ ተኛች።ዮርዲ ደግሞ ወንድሙን ለማወቅ ጓጉቶ ሲያስብ አመሼ።ቤዛም ምን አለበት ሴት በሆነች ማለቷ አልቀረም ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እሁድ ከሰዐት በኋላ ......................................
ቃለአብ ዝንጥ ብሏል የሚለው ቃል አይገልፀውም።አረ እማዬ ምንድን ነው ምስራቹን ንገሪኝ አለ።
"ወይ አንተ ደግሞ፤በቃ እሺ አባትና እህት ወንድምህን ልትተዋወቅ ነው"ብላ አበሰረችው
"ቃለአብ በደስታ ዘሎ እናቱ ላይ ተጠመጠመባት።ጉንጯን እያገላበጠ በደስታ ሳማት።
ከሁሉም በላይ ወንድሙን ለማወቅ ቋመጠ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እነ ወይዘሮ አለም ቤቱን ሞቅ ደመቅ አድርገው ምግቡን በእየፈርጁ ሰርተው እንግዶቹን እየጠበቁ ነው።ዮርዲም እንደ ቤተሰብ አባል የሚቆጠረውን ደሴን እውነቱን ነግሮት ከዮርዲ ጋር እሚሆነውን እየጠበቁ ነው።
በር ተንኳኳ ሁሉም ከመቀመጫቸው ተነሱ።እልፍነሽ በሩን ከፈተች።እናት እና ልጅ ገቡ ።ሳሎን በር ላይ እንደደረሱ ቃለአብ ከዮርዳኖስ እና ከደሴ ጋር አይን ለአይን ተጋጨ።ዮርዲ ድንገት ልቡ ቀጥ ስትል ተሰማው።በህይወት ዘመኑ እንኳን ይሔንን ያክል የደነገጠበትን ቀን አያስታውስም።ቃለአብም ልቡ ከዳችው ደነገጠ ልቡን በእጁ ያዘ።ደሴ የዮርዳኖስን ህልም እና ወንድማማችነት እያያያዘ አግራሞት ተሞልቷል።
ዮርዳኖስ ሮጦ ቃለአብ ወንድሜ አለ ቃለአብም ዮርዲዬ አለ ተቃቀፋ።ህልም አይደለም አይደል ቃል አለ ዮርዲ ።አንተን ልጠይቅህ ወንድሜ እየቃዠሁ አይደለም አለ ጥያቄውን በጥያቄ እየደገመ።
ሙሉ ቤተሰቡ ተዋወቀ።ቃለአብ ተሾመ እና ዮርዳኖስ ተሾመ ከሁለት ማህፀን ግን በአንድ ቀን የተወለዱ የሁለት ማህፀን መንትዮች።

ይቀጥላል

@Ethio_leboled #Share
❥❥________⚘_______❥❥


>>Click here to continue<<

Ahadu picture




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)