TG Telegram Group & Channel
Ahadu picture | United States America (US)
Create: Update:

😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

🔥ክፍል 20

ደራሲ ዮሴፍ ተሾመ
.
.
.
ቃልና ዮርዳኖስ እስከ ስድስት ሰዐት ድረስ ሲጫወቱ ከቆዩ በኋላ ስድስት ሰዐት ላይ ሔዋን ደወለች።ሚስቴ ነች የደለወለችው ቃል አንዴ ላናግር አለ ዮርዲ በሹፈት ቃለአብን እያስፈቀደው።
"ሔሎ ሳልሳዊት"አለ ዮርዲ
"ዮርዳኖስ ከስራ ወጥቻለሁ ላግኝህ"አለች
ዮርዲ በሙሉ ስሙ ጠርታው የማታውቀው ልጅ ዮርዳኖስ ብላ ስትጠራው መገረሙ አልቀረም "አሁን ራቅ ብያለሁ ግን በ 40 ደቂቃ ውስጥ እደርሳለሁ እደውልልሻለሁ ፍቅር"ብሎ ስልኩን ዘጋው።
"በል ና ሸኘኝ"አለ ዮርዲ
ዮርዲ ማርዘነብን አመስግኖ በድንጋጤ ላይ ሌላ ድንጋጤ ጨምሮባት ወጣ።
ቃለአብ እየሸኘው "ስማ ሚስትህን መች ነው እምታስተዋውቀኝ"አለ ቃል
"እንዴ አታስብ፣ይልቁንስ በስልክ አንድ ልጅ እንደወደድክ ነግረኸኝ ነበር አለ"ዮርዲ ለወሬ መጀመሪያ
"አረ ተወው ዮርዲዬ ባክህ ፍቅረኛ አላት"አለ ቃል
"እና ፍቅረኛ ካላትማ......"ሲል ዮርዲ ቃለአብ ከአፋ ነጠቀው
"አዎ ፍቅረኛ አላት ግን ደግሞ ታፈቅረኛለች"አለ ቃል
"ማለት እስኪ ግልፅ አድርገው ?"አለ ዮርዲ
"ስማ እኔ እንጃ ከስንቱ እንደምመሳሰል።ይኸው ከአንተ ጋር እመሳሰላሁ።ከልጅቷ ፍቅረኛም ጋር እንደዚሁ"አለና ፈገግ ብሎ ቀጠለ "እየውልህ ልጁን ትወደዋለች እንደምታፈቅረው ግን እንኳን እኔ እሷም እርግጠኛ አይደለችም።እኔን ደግሞ በእርግጠኝነት ታፈቅረኛለች።እሱ በቀለበት አስሯት እንጂ ልቧን በፍቅር አላሰረውም"አለ ቃል
"እና ልጁ ይህን ያውቃል"
"አይመስለኝም"አለ ግን አንተ ምን ትመክረኛለህ?"አለ ቃል
"ምን መሰለህ እውነት ነው እማታፈቅረው ከሆነ ቃልኪዳን አለብኝ ብላ አብራው መሆን የለባትም።እንዲያውም ትልቅ ሀጢያት የሚሆንባት ሌላ ማፍቀሯ ሳይሆን ሳታፈቅረው ለቃልኪዳን ብቻ ብላ አብራው ብትሆን ነው።ግን እውነቱን ለልጁ መነገር አለበት" አለ ዮርዲ
"ልክ ነህ"አለ ቃል ንግግሩን እንዲቀጥል በሚገፋ መልኩ
"አየህ አንዳንድ ሰዎች በአመታት አብሮ መኖር ውስጥ መላመድን ይፈጥሩና የምር የተፋቀሩ መስሏቸው ፍቅር ይመሰርታሉ አልፎም ትዳር ይመሰርታሉ።ነገር ግን ትዳራቸው አይሰምርም።ምክንያቱም ልባቸው ውስጥ ያለው ፆታዊ ፍቅር ሳይሆን የእህትና የወንድምነት አይነት ሆኖ አልጋም ላይ ሆነ ኑሯቸው ላይ ስሜት አልባኝነት ይፈጠራል።ምን አልባትም አንተ የምትለኝ ልጅ ላይ ያለው ነገር ይሔ ሊሆን ይችላል።ነገር ግን ልቧን አድምጣ ልቧ የሚላትን ለመከተል እንዲበጃት ጊዜ ስጣት" አለ ዮርዲ
"ልክ ብለሀል እሷም ይሔንን ነው ያለችኝ ጊዜ ስጠኝ አትቅረበኝ ብቻየን ሆኘ ማሰብ እፈልጋለሁ ነው የለችኝ"አለ ቃል
"ጥሩ ነው ይሳካልህ ወንድሜ ደስታህ ደስታዬ ነው።ለማንኛውም ደሳለኝ ነገ ይመጣል።ነግሮሀል?"አለ ዮርዲ
"ደውየለት ነበር እኔም መምጣቱን በጉጉት እየጠበኩ ነው"አለ ቃል።
ቃለአብ ዮርዲን ግማሽ መንገድ ከሸኘው በኋላ በል ሚስትህን አግኝ ወንድሜ ነገ አብረን ደሴን እንቀበለዋለን ብሎ ተሰናብቶት ተመለሰ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ሔዋን እና ዮርዲ ፍቅራቸው ፈገግ ብሎበት በነበረው ዋርካ ላይ ሔደው አረፍ አሉ።ዮርዲ ሔዋን ላይ ብዙ የተቀየሩ ነገሮች እንዳሉ ታዝቧል።ቀለበቱ ከእጇ ላይ የለም ሀብሉ ከአንገቷ ላይ የለም።ደንግጦ ሲጠይቃት ጠፋብኝ አለች።እውነታው ግን ከዛ የራቀ ነው።ግራ ተጋብታ መወሰን አቅቷት ነው።የዮርዳኖስን ቃልኪዳን ቃለአብ ሰብሮታል።በቃለአብ ፍቅር የዮርዳኖስ ቀለቀት ከሔዋን እጅ ላይ አፈትልኮ ወደቀ።ይህ ነው እውነታው።
ሔዋን ግራ ተጋብታ ግራ እያጋባችው ነው።የጠየቃትን እረስታ ሌላ ትመልሳለች በራሷ አለም ውሰጥ ንጉድ ብላለች።"ዮርዲ ብዙ የሆነልኝ ንፁህ አፍቃሪየን ቃሉን በላሁ።ከፊቱ መቆም የማይገባኝ ርካሽ ሰው ነኝ ትልና ደግሞ እንደገና ልቤ የፈቀደውን ነው የመረጥኩት ምን አጠፋሁ" እያለች አራሷን እየሞገተች ከዮርዳኖስ ጋር አካሏ አለ እንጂ መንፈሷ ጭልጥ ብሎ ሔዷል።
"ሔዋን ምን ሆነሽ ነው?"ብሎ ዮርዲ ከሀሳብ መለሳት ።
"ልክ ነኝ አይደል አዎ ትክክለኛ ውሳኔ ነዉ"አለች ያልተጠየቀችውን
"እንዴ ሒዊ ምንድነው የሆንሽው?አሞሻል እንዴ?"አለ ዮርዲ
"አየሰ ስለ ስራ እያሰብኩ ነው"ደና ነኝ አለች
"እንደዚህ እስክትሆኝ? እምትሰሪ እኮ ለስጋሽ ነው።ስራው ከአንቺ ይበልጣል?መተው አለብሽ"አለ ዮርዲ እየተጨነቀ
"ዮርዳኖስ ደና ነኝ አታስብ"አለች
ይሔ ሙሉ ስሙን መጥራቷ ቢከፋውም ዋጥ አድርጎ "ሒዊ ያኔ ስትሔጅ የሰጠሽኝን ስጦታ ሀብል አንቺ አንገቴ ላይ እስክታጠልቂኝ ድረስ እጄ ጋር ነበር።አሁን አንቺ ታደርጊልኛለሽ"አለ በፍቅር አይን አይኗን እያየ
"አይ እጅህ ጋር ያምራል እንዲሁ ይቀመጥ"አለች
"እሺ ታዛዥ ነኝ እመቤቴ" ብሎ ሊስማት ሲጠጋ ጉንጯን ሰጠችው
እሷም ደስ እንዲለው ብላ ጉንጩን ሳመችው እና በል ወደ ስራ መሔድ አለብኝ ሰላሳ ደቂቃ አሳልፊያለሁ አለች ለመሄድ እየተነሳች....

አቶ ተሾመ ከደብረ ማርቆስ ከተመለሰ በኋላ ምንም ጥሩ ስሜት እየታየበት አይደለም።ከራሱ ጋር ያወራል።ወይዘሮ አለም ምን ሆነህ ነው ስትለው መልስ አይመልስም።አረ እንዲውም ዘግቷቸዋል።የማታ ማታ የግዱን "አንተ ዮርዲ ከደሴ ውጭ ሌላ ጓደኛ አለህ አይደል?አለ አቶ ተሾመ
"አባየ ከጓደኛም በላይ ወንድሜ ነው።ቃለአብ ተሾመ ይባላል የሚገርመው ያባታችን ስም ብቻ አይደለም የሚመሳስለው መልካችን እና የተወለድንበት ቀን ወር እድሚአችንም ሁሉ ተመሳሳይ ነው"አለ ዮርዲ ከስልኩ ላይ የቃልን ፎቶ እየፈለገ።
አቶ ተሾመ የበለጠ ተረበሸ።
"አባዬ ምነው ልጁን ታውቀዋለህ እንዴ?መጥፎ ልጅ ነው?ለምን ተረበሽክ?"አለች ቤዛ
አቶ ተሾመ ግን ምንም መልስ አልሰጠም።ዮርዲም ከስልኩ ላይ የቃልን ፎቶ እያሳየው "እየው እስኪ አንመሳሰልም?"አለ ዮርዲ
"እሚገርም ነው ወንድማማቾች ነው እምትመስሉት።የት ነው የተዋወቃችሁ?" አለ አቶ ተሾመ
"በህልሜ ነው አባ ቤዛ ይሔ መንታ ወንድምህ ነው ብላ አስተዋወቀችኝ።ከዚህ በፊት አላውቀውም ነበር ከዛም ተዋወቅን እሱም ወንድሙ እንደምመስለው ነገረኝ"አለ ዮርዲ
"ፃድቃን ሳይቀጣጠሩ ይገናኛሉ ማለት ይሔ ነው"አለ አቶ ተሾመ
"አንተ ሰውየ ምን ሆነሀል ድካም ነው በቃ ግባና አረፍ በል"አለች ወይዘሮ አለም።
"አይ ግዴለም ይልቁንስ አሁን የፊታችን እሁድ እንግዶች ይመጡብናል ተዘጋጁ አለምየ"አለ አቶ ተሾመ
"የምን እንግዳ?"አለች ወይዘሮ አለም
"እሱ ይሰደርሳል እናተ ተዘጋጁ"አለ
"እኔ እምለው ቆይ የኔና የሔዋንን ፎቶ ከሳሎን የት አደረሳችሁት"አለ ዮርዲ
"ምን ቤዛ ስታፀዳ ተሰበረ ምኝታ ቤት ቁም ሳጥኑ ጋር አለ"አለች ወይዘሮ አለም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ማህበረ ትጉሃን ቢሮ ውስጥ ብዙ አዳዲስ ሰዎች እየገቡ ነው።ስራቸውን እያጧጧፉ ነው።በወረዳው ወስጥ ሶስት ሀይስኩሎች በማህበረ ትጉሀን እየተገነቡ ነው።በተሰጣቸው ቦታ ላይ ብሎኮችን ጨምረው ገንብተው ወደ ሶስት መቶ የሚደርሱ አረጋውያንን እየጦሩ ነው።ወላጅ አልባ ዘጠና ህፃናትን ይዘዋል።በመጭው መስክረም ትምህርት ሊያስገቧቸው እቅድ ይዘዋል።በትግራይ ክልል በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር እርዳታ ሰጥተው በፌዴራል ደረጃ የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።ሁሉም አባል ፍፁም በሆነ ታዐማኒነት እና በፍቅር ነው እሚሰራው።
ምናሴ እርዳታ እሚሰጥባቸውን አካባቢዎች ለማጥናት ከሔኖክ ጋር መላ ኢትዮጵያን እያካለለ ነው።
"እንዴት አደርሽ ሒዊ"አለና ቃል ጉንጯን ሳም አደረጋት
"ቃል እንዴት ነህ?"አለች ኮምፒውተሩ ላይ

😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

🔥ክፍል 20

ደራሲ ዮሴፍ ተሾመ
.
.
.
ቃልና ዮርዳኖስ እስከ ስድስት ሰዐት ድረስ ሲጫወቱ ከቆዩ በኋላ ስድስት ሰዐት ላይ ሔዋን ደወለች።ሚስቴ ነች የደለወለችው ቃል አንዴ ላናግር አለ ዮርዲ በሹፈት ቃለአብን እያስፈቀደው።
"ሔሎ ሳልሳዊት"አለ ዮርዲ
"ዮርዳኖስ ከስራ ወጥቻለሁ ላግኝህ"አለች
ዮርዲ በሙሉ ስሙ ጠርታው የማታውቀው ልጅ ዮርዳኖስ ብላ ስትጠራው መገረሙ አልቀረም "አሁን ራቅ ብያለሁ ግን በ 40 ደቂቃ ውስጥ እደርሳለሁ እደውልልሻለሁ ፍቅር"ብሎ ስልኩን ዘጋው።
"በል ና ሸኘኝ"አለ ዮርዲ
ዮርዲ ማርዘነብን አመስግኖ በድንጋጤ ላይ ሌላ ድንጋጤ ጨምሮባት ወጣ።
ቃለአብ እየሸኘው "ስማ ሚስትህን መች ነው እምታስተዋውቀኝ"አለ ቃል
"እንዴ አታስብ፣ይልቁንስ በስልክ አንድ ልጅ እንደወደድክ ነግረኸኝ ነበር አለ"ዮርዲ ለወሬ መጀመሪያ
"አረ ተወው ዮርዲዬ ባክህ ፍቅረኛ አላት"አለ ቃል
"እና ፍቅረኛ ካላትማ......"ሲል ዮርዲ ቃለአብ ከአፋ ነጠቀው
"አዎ ፍቅረኛ አላት ግን ደግሞ ታፈቅረኛለች"አለ ቃል
"ማለት እስኪ ግልፅ አድርገው ?"አለ ዮርዲ
"ስማ እኔ እንጃ ከስንቱ እንደምመሳሰል።ይኸው ከአንተ ጋር እመሳሰላሁ።ከልጅቷ ፍቅረኛም ጋር እንደዚሁ"አለና ፈገግ ብሎ ቀጠለ "እየውልህ ልጁን ትወደዋለች እንደምታፈቅረው ግን እንኳን እኔ እሷም እርግጠኛ አይደለችም።እኔን ደግሞ በእርግጠኝነት ታፈቅረኛለች።እሱ በቀለበት አስሯት እንጂ ልቧን በፍቅር አላሰረውም"አለ ቃል
"እና ልጁ ይህን ያውቃል"
"አይመስለኝም"አለ ግን አንተ ምን ትመክረኛለህ?"አለ ቃል
"ምን መሰለህ እውነት ነው እማታፈቅረው ከሆነ ቃልኪዳን አለብኝ ብላ አብራው መሆን የለባትም።እንዲያውም ትልቅ ሀጢያት የሚሆንባት ሌላ ማፍቀሯ ሳይሆን ሳታፈቅረው ለቃልኪዳን ብቻ ብላ አብራው ብትሆን ነው።ግን እውነቱን ለልጁ መነገር አለበት" አለ ዮርዲ
"ልክ ነህ"አለ ቃል ንግግሩን እንዲቀጥል በሚገፋ መልኩ
"አየህ አንዳንድ ሰዎች በአመታት አብሮ መኖር ውስጥ መላመድን ይፈጥሩና የምር የተፋቀሩ መስሏቸው ፍቅር ይመሰርታሉ አልፎም ትዳር ይመሰርታሉ።ነገር ግን ትዳራቸው አይሰምርም።ምክንያቱም ልባቸው ውስጥ ያለው ፆታዊ ፍቅር ሳይሆን የእህትና የወንድምነት አይነት ሆኖ አልጋም ላይ ሆነ ኑሯቸው ላይ ስሜት አልባኝነት ይፈጠራል።ምን አልባትም አንተ የምትለኝ ልጅ ላይ ያለው ነገር ይሔ ሊሆን ይችላል።ነገር ግን ልቧን አድምጣ ልቧ የሚላትን ለመከተል እንዲበጃት ጊዜ ስጣት" አለ ዮርዲ
"ልክ ብለሀል እሷም ይሔንን ነው ያለችኝ ጊዜ ስጠኝ አትቅረበኝ ብቻየን ሆኘ ማሰብ እፈልጋለሁ ነው የለችኝ"አለ ቃል
"ጥሩ ነው ይሳካልህ ወንድሜ ደስታህ ደስታዬ ነው።ለማንኛውም ደሳለኝ ነገ ይመጣል።ነግሮሀል?"አለ ዮርዲ
"ደውየለት ነበር እኔም መምጣቱን በጉጉት እየጠበኩ ነው"አለ ቃል።
ቃለአብ ዮርዲን ግማሽ መንገድ ከሸኘው በኋላ በል ሚስትህን አግኝ ወንድሜ ነገ አብረን ደሴን እንቀበለዋለን ብሎ ተሰናብቶት ተመለሰ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ሔዋን እና ዮርዲ ፍቅራቸው ፈገግ ብሎበት በነበረው ዋርካ ላይ ሔደው አረፍ አሉ።ዮርዲ ሔዋን ላይ ብዙ የተቀየሩ ነገሮች እንዳሉ ታዝቧል።ቀለበቱ ከእጇ ላይ የለም ሀብሉ ከአንገቷ ላይ የለም።ደንግጦ ሲጠይቃት ጠፋብኝ አለች።እውነታው ግን ከዛ የራቀ ነው።ግራ ተጋብታ መወሰን አቅቷት ነው።የዮርዳኖስን ቃልኪዳን ቃለአብ ሰብሮታል።በቃለአብ ፍቅር የዮርዳኖስ ቀለቀት ከሔዋን እጅ ላይ አፈትልኮ ወደቀ።ይህ ነው እውነታው።
ሔዋን ግራ ተጋብታ ግራ እያጋባችው ነው።የጠየቃትን እረስታ ሌላ ትመልሳለች በራሷ አለም ውሰጥ ንጉድ ብላለች።"ዮርዲ ብዙ የሆነልኝ ንፁህ አፍቃሪየን ቃሉን በላሁ።ከፊቱ መቆም የማይገባኝ ርካሽ ሰው ነኝ ትልና ደግሞ እንደገና ልቤ የፈቀደውን ነው የመረጥኩት ምን አጠፋሁ" እያለች አራሷን እየሞገተች ከዮርዳኖስ ጋር አካሏ አለ እንጂ መንፈሷ ጭልጥ ብሎ ሔዷል።
"ሔዋን ምን ሆነሽ ነው?"ብሎ ዮርዲ ከሀሳብ መለሳት ።
"ልክ ነኝ አይደል አዎ ትክክለኛ ውሳኔ ነዉ"አለች ያልተጠየቀችውን
"እንዴ ሒዊ ምንድነው የሆንሽው?አሞሻል እንዴ?"አለ ዮርዲ
"አየሰ ስለ ስራ እያሰብኩ ነው"ደና ነኝ አለች
"እንደዚህ እስክትሆኝ? እምትሰሪ እኮ ለስጋሽ ነው።ስራው ከአንቺ ይበልጣል?መተው አለብሽ"አለ ዮርዲ እየተጨነቀ
"ዮርዳኖስ ደና ነኝ አታስብ"አለች
ይሔ ሙሉ ስሙን መጥራቷ ቢከፋውም ዋጥ አድርጎ "ሒዊ ያኔ ስትሔጅ የሰጠሽኝን ስጦታ ሀብል አንቺ አንገቴ ላይ እስክታጠልቂኝ ድረስ እጄ ጋር ነበር።አሁን አንቺ ታደርጊልኛለሽ"አለ በፍቅር አይን አይኗን እያየ
"አይ እጅህ ጋር ያምራል እንዲሁ ይቀመጥ"አለች
"እሺ ታዛዥ ነኝ እመቤቴ" ብሎ ሊስማት ሲጠጋ ጉንጯን ሰጠችው
እሷም ደስ እንዲለው ብላ ጉንጩን ሳመችው እና በል ወደ ስራ መሔድ አለብኝ ሰላሳ ደቂቃ አሳልፊያለሁ አለች ለመሄድ እየተነሳች....

አቶ ተሾመ ከደብረ ማርቆስ ከተመለሰ በኋላ ምንም ጥሩ ስሜት እየታየበት አይደለም።ከራሱ ጋር ያወራል።ወይዘሮ አለም ምን ሆነህ ነው ስትለው መልስ አይመልስም።አረ እንዲውም ዘግቷቸዋል።የማታ ማታ የግዱን "አንተ ዮርዲ ከደሴ ውጭ ሌላ ጓደኛ አለህ አይደል?አለ አቶ ተሾመ
"አባየ ከጓደኛም በላይ ወንድሜ ነው።ቃለአብ ተሾመ ይባላል የሚገርመው ያባታችን ስም ብቻ አይደለም የሚመሳስለው መልካችን እና የተወለድንበት ቀን ወር እድሚአችንም ሁሉ ተመሳሳይ ነው"አለ ዮርዲ ከስልኩ ላይ የቃልን ፎቶ እየፈለገ።
አቶ ተሾመ የበለጠ ተረበሸ።
"አባዬ ምነው ልጁን ታውቀዋለህ እንዴ?መጥፎ ልጅ ነው?ለምን ተረበሽክ?"አለች ቤዛ
አቶ ተሾመ ግን ምንም መልስ አልሰጠም።ዮርዲም ከስልኩ ላይ የቃልን ፎቶ እያሳየው "እየው እስኪ አንመሳሰልም?"አለ ዮርዲ
"እሚገርም ነው ወንድማማቾች ነው እምትመስሉት።የት ነው የተዋወቃችሁ?" አለ አቶ ተሾመ
"በህልሜ ነው አባ ቤዛ ይሔ መንታ ወንድምህ ነው ብላ አስተዋወቀችኝ።ከዚህ በፊት አላውቀውም ነበር ከዛም ተዋወቅን እሱም ወንድሙ እንደምመስለው ነገረኝ"አለ ዮርዲ
"ፃድቃን ሳይቀጣጠሩ ይገናኛሉ ማለት ይሔ ነው"አለ አቶ ተሾመ
"አንተ ሰውየ ምን ሆነሀል ድካም ነው በቃ ግባና አረፍ በል"አለች ወይዘሮ አለም።
"አይ ግዴለም ይልቁንስ አሁን የፊታችን እሁድ እንግዶች ይመጡብናል ተዘጋጁ አለምየ"አለ አቶ ተሾመ
"የምን እንግዳ?"አለች ወይዘሮ አለም
"እሱ ይሰደርሳል እናተ ተዘጋጁ"አለ
"እኔ እምለው ቆይ የኔና የሔዋንን ፎቶ ከሳሎን የት አደረሳችሁት"አለ ዮርዲ
"ምን ቤዛ ስታፀዳ ተሰበረ ምኝታ ቤት ቁም ሳጥኑ ጋር አለ"አለች ወይዘሮ አለም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ማህበረ ትጉሃን ቢሮ ውስጥ ብዙ አዳዲስ ሰዎች እየገቡ ነው።ስራቸውን እያጧጧፉ ነው።በወረዳው ወስጥ ሶስት ሀይስኩሎች በማህበረ ትጉሀን እየተገነቡ ነው።በተሰጣቸው ቦታ ላይ ብሎኮችን ጨምረው ገንብተው ወደ ሶስት መቶ የሚደርሱ አረጋውያንን እየጦሩ ነው።ወላጅ አልባ ዘጠና ህፃናትን ይዘዋል።በመጭው መስክረም ትምህርት ሊያስገቧቸው እቅድ ይዘዋል።በትግራይ ክልል በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር እርዳታ ሰጥተው በፌዴራል ደረጃ የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።ሁሉም አባል ፍፁም በሆነ ታዐማኒነት እና በፍቅር ነው እሚሰራው።
ምናሴ እርዳታ እሚሰጥባቸውን አካባቢዎች ለማጥናት ከሔኖክ ጋር መላ ኢትዮጵያን እያካለለ ነው።
"እንዴት አደርሽ ሒዊ"አለና ቃል ጉንጯን ሳም አደረጋት
"ቃል እንዴት ነህ?"አለች ኮምፒውተሩ ላይ


>>Click here to continue<<

Ahadu picture




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)