Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/hottg/post.php on line 59

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/2024-05-29/post/wegoch/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/hottg/post.php on line 72
ማህተብ ፈቶ ቀለበት ማሰር የለም! @ወግ ብቻ
TG Telegram Group & Channel
ወግ ብቻ | United States America (US)
Create: Update:

ማህተብ ፈቶ ቀለበት ማሰር የለም!

'አጅሬ' የምለው...'ጊዜዬ' የሚለኝ አንድ ጌታን የተቀበለ የከንፈር ወዳጅ ነበረኝ።አብሮነታችን ዕድሜ ላይኖረው...ማህተቤን ላልፈታ...ማህተብ ላያስር ነገር...ከማይካደው እውነታ በላይ ብዙ ነገሩ ገዝቶኝ አብሬው መጓዝ ጀመርኩ።ተገኝቼ 'ማላውቅበት ቦታ ከሱ ጋር ተገኘሁ...ስጋ እየፆምኩ ስጋ የበላ እሱን ለመሳም አልግደረደርም ነበር።አንገቱ እስኪዥጎረጎር መጥጬው 'ከጠየቁህ ጊዜ ናት በል' ስል ግዳይ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር።ያውም በሁዳዴ...ያውም በአቢዩ!
ያወቅሁትኝ ሰሞን የሴት ግሳንግሴን ገፍፌ ጥዬ...እኔው ደዋይ...እኔው መልዕክት ላኪ...እኔው አጥብቆ ጠያቂ እየሆንኩ በእናትነት እና በሚስትነት መሃል የሚቀላውጥ ማንነቴን ጋትኩት።ሰከረ...ስካሩ ዕድሜ ገዛ።
በሱ ካስተናገድኳቸው እብደቶቼ ሁሉ የማልረሳው የlipstickኬን ነገር ነው።አንድ ዕለት አክስቴን ልጎበኝ በሄድኩበት lipstickኬ ማለቁ ትዝ ብሎኝ የአክስቴን ልጅ ግዥልኝ ብዬ መላክ...ዘምናኒት ጁስ ጁስ የሚል lipstick ገዝታ መምጣት...ልቀባው ወደ አፌ ሳስጠጋው የጠረኑ ማማር...ተቀብቼ ስቀምሰው የጣዕሙ ነገር...ቴዲ "ሳሙኝ ሳሙኝ የሚል ከንፈር..."ያለው አምለሰት ይኸን መሳይ ተቀብታ ብትጠጋው ነው ብዬ እንድደመድም አደረገኝ። 'ቴዲ አንጋጦ ባየው ከንፈር እንዲህ አጉል ከሆነ አጅሬ ቁልቁል አይቶኝማ እንደምን አይስት!'የሚል ሔዋናዊ ሀሳብ ብልጭ አለብኝና ያንን እንጆሪ እንጆሪ የሚል lipstick አልጋዬ ላይ አስቀምጬ ኩሽና ገባሁ።ከኩሽና ስመለስ እማይበጃችሁ ይድረቅና ድርርርርርቅ ብዬ ቀረሁ...አንድ ከየት እንደመጣ የማላውቀው(በኋላ ሳጣራ የአክስቴ ሰራተኛ ልጅ) በግምት 3 አመት የሚሆነው ህፃን lipstickኬን ይዞ ይመጠምጣል።በድንጋጤ ነጥቄ ስመለከተው እንኳን የሚቀባ የሚታይ የለውም።ህፃኑን አየሁት...የጠባውን ያጣጥማል...'ደሜ ፈላ' ብል ደሜ ራሱ ይታዘበኛል...ተንተከተከ...ተፈናጥሮ ሰው እስኪጠብስ! የሆነ ስላችሁ የጨረሳችሁት ሁነት...በምናባችሁ እንዳማረ ተጀምሮ እንዳማረ የሚጠናቀቅ ሁነት...ሊሆን እንደማይችል ስታውቁት ልባችሁ ይወርድ የለ?እኔ ሁለመናዬ ነው የወረደው...ከእንጥሌ ጀምሮ... ልጁን በልቤ ረገምኩት...
'ከንፈርክን ስማ 'እንደ ወንድሜ ነው 'ማይህ ' ትበልህ'...'አልጋ አስይዛ ፔሬድ ላይ ነኝ ትበልህ!'... 'ፔሬዱ ሲሄድ 'ትንሽ ነው' ትበልህ' ብዬው ሳበቃ
"ቤቢ አሜን በል" አልኩት።
"አሜን"...ኤታባቱ!

እናም እኔ ወለተ ማርያም...የአብማይቱ ማርያም ልጅ...የማርቆሷ ሎጋ...ጠላታችሁን የሎስ ያክንፈውና አስተካክሎ 'ነገ' እንኳን ማለት ከማይችል ደቡቤ ጋር ከነፍኩ።ዘረኛ ነበርኩ...እልልልም ያልኩ ዘረኛ!ወንድ ጎጃሜ ካልሆነ ወንድ የማይመስለኝ!'ሲያናድደኝ የምሰድበው ስድብ እንኳን ካልገባው ምን ላደርገው ነው?' ብዬ የምራቀቂቱ...
''መቼ ይመችሃል?'' ስለው
"ነጌ"
"እንዴት አርገህ አበጃጀኸው?" ስለው
"እንደዚህ እንደዚህ 'አርግቼ' "
"እኔ ኦርቶዶክስ...አንተ ጴንጤ...በምን ስሌት አብረን እንሁን?"ስለው
" 'እምነት...ተስፋ...ፍቅር እነዚህ ሶስቱ ፀንተው ይኖራሉ፤ከሁሉም ግን ፍቅር ይበልጣል' ነው መፅሐፍ ቅዱስ 'የምለው' " ከሚለኝ አንድ ተላሰስ ጋር...ወደቅሁ።
መላመዳችን ሲበረታ...ቅርርባችን ልክ ሲያጣ ጥያቄዎቻችንን ሽሽት ገባን።መሄድ ብቻ!እስከሆነ ቀይ መስመር ድረስ...በድፍረት ጥያቄዎቻችንን ስር ድረስ የማንጠያየቀው የማይቀረውን መለያየት ያራቅን መስሎን ነበር።ጠንካራ አማኝም ባልሆን ፈሪ ነኝ...ነፍስ አባቴ ዘንድ ስከንፍ ሄጄ 'መናፍቅ ወድጄ ልቤ ጠፋ' አልኳቸው።
"ወለቴ"
"ኧይ አባ"
"እምን ድረስ ቀረብሽው?"
"ሲሉኝ?"
"ተመተቃቀፍ አለፋችሁ?" ሲሉኝ መሽኮርመም
"ወለቴ...አደራሽን አረከሰኝ እንዳትይኝ"
"ይፍቱኝ አባ"
"አዪዪዪዪዪ....አይ ወለቴ...ምነው?ህጉን ስታውቂው?" አሉኝ...የምፈታበት መፅሐፍ ተነበበ...ለሶስት ተከታታይ ቀናት ጠመቁኝ።
ህጉ 'ከአህዛብ አትጠጉ' ይላል...እንኳን አንሶላ መጋፈፍ...ማዕድ መካፈልን ያወግዛል...ግን ከህግ በላይ የሚገዛ፣ከውግዘት በላይ የሚያስር መሳሳብ ሲመጣስ?ምኔንም መሰሰት እስካልችል ከተሸነፍኩስ?አጅሬ አንዴ የሆነ መጣጥፍ ሲያነብልኝ "ሰው ከፍቅር የሚቆራረጠው ሰጥቶ መቀበልን ሲሻ ነው...የፍቅር ምክንያቱም ውጤቱም መስጠት ነው...ስለፍቅር የሚደረጉ ዝቅታዎች ሁሉ ከየትኛውም ከፍታ ይልቃሉ...ፍቅር ውስጥ መቀበልን የሚሻ እሱ ቀሽም ነው..." ብሎኝ ነበር።ያለስስት ስለሰጠሁት ሁሉ ደስተኛ ነኝ...አይደፈርን ደፍሬ፣አይተላለፉትን ተላልፌም...ይናፍቀኛል።
በስተ መጨረሻ...ተመርቆ ከጊቢ ሊወጣ ሳምንት ሲቀረው
"ተጠመቅና ከመሄድህ በፊት እንጋባ" ብዬ እስከምመረቅ ያሉትን ሶስት አመታት በዕምነት ልጠብቀው መዘጋጀቴን ነገርኩት...'ያዲያቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም' እንዲሉ
"አንቺ ወደኔ እንዳትመጪ ምንድነው 'ሚያግድሽ? ቤተሰብ ነው?''አለኝ።እርግጥ ነው ቤተሰቦቼ የሚያማልደውን እየሱስ እየመገቡ አላሳደጉኝም...ከነሱ በላይ ግን...ነጌ ምጤ ሲመጣ ማን ሊያዋልደኝ?ማን ጭንቄን ሊያረግብ?የሱ ቀበቶ በቂ አልነበረምና ልቤን ዳር እስከዳር እየከረሰሰኝ...ዘለዓለም የሚመስል ፅልመት እየወረሰኝ...ሸኘሁት...ማህተብ ፈቶ ቀለበት ማሰር የለም።

ዘማርቆስ
29/08/16

By @gize_yayeh

@wegoch
@wegoch
@paappii

ማህተብ ፈቶ ቀለበት ማሰር የለም!

'አጅሬ' የምለው...'ጊዜዬ' የሚለኝ አንድ ጌታን የተቀበለ የከንፈር ወዳጅ ነበረኝ።አብሮነታችን ዕድሜ ላይኖረው...ማህተቤን ላልፈታ...ማህተብ ላያስር ነገር...ከማይካደው እውነታ በላይ ብዙ ነገሩ ገዝቶኝ አብሬው መጓዝ ጀመርኩ።ተገኝቼ 'ማላውቅበት ቦታ ከሱ ጋር ተገኘሁ...ስጋ እየፆምኩ ስጋ የበላ እሱን ለመሳም አልግደረደርም ነበር።አንገቱ እስኪዥጎረጎር መጥጬው 'ከጠየቁህ ጊዜ ናት በል' ስል ግዳይ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር።ያውም በሁዳዴ...ያውም በአቢዩ!
ያወቅሁትኝ ሰሞን የሴት ግሳንግሴን ገፍፌ ጥዬ...እኔው ደዋይ...እኔው መልዕክት ላኪ...እኔው አጥብቆ ጠያቂ እየሆንኩ በእናትነት እና በሚስትነት መሃል የሚቀላውጥ ማንነቴን ጋትኩት።ሰከረ...ስካሩ ዕድሜ ገዛ።
በሱ ካስተናገድኳቸው እብደቶቼ ሁሉ የማልረሳው የlipstickኬን ነገር ነው።አንድ ዕለት አክስቴን ልጎበኝ በሄድኩበት lipstickኬ ማለቁ ትዝ ብሎኝ የአክስቴን ልጅ ግዥልኝ ብዬ መላክ...ዘምናኒት ጁስ ጁስ የሚል lipstick ገዝታ መምጣት...ልቀባው ወደ አፌ ሳስጠጋው የጠረኑ ማማር...ተቀብቼ ስቀምሰው የጣዕሙ ነገር...ቴዲ "ሳሙኝ ሳሙኝ የሚል ከንፈር..."ያለው አምለሰት ይኸን መሳይ ተቀብታ ብትጠጋው ነው ብዬ እንድደመድም አደረገኝ። 'ቴዲ አንጋጦ ባየው ከንፈር እንዲህ አጉል ከሆነ አጅሬ ቁልቁል አይቶኝማ እንደምን አይስት!'የሚል ሔዋናዊ ሀሳብ ብልጭ አለብኝና ያንን እንጆሪ እንጆሪ የሚል lipstick አልጋዬ ላይ አስቀምጬ ኩሽና ገባሁ።ከኩሽና ስመለስ እማይበጃችሁ ይድረቅና ድርርርርርቅ ብዬ ቀረሁ...አንድ ከየት እንደመጣ የማላውቀው(በኋላ ሳጣራ የአክስቴ ሰራተኛ ልጅ) በግምት 3 አመት የሚሆነው ህፃን lipstickኬን ይዞ ይመጠምጣል።በድንጋጤ ነጥቄ ስመለከተው እንኳን የሚቀባ የሚታይ የለውም።ህፃኑን አየሁት...የጠባውን ያጣጥማል...'ደሜ ፈላ' ብል ደሜ ራሱ ይታዘበኛል...ተንተከተከ...ተፈናጥሮ ሰው እስኪጠብስ! የሆነ ስላችሁ የጨረሳችሁት ሁነት...በምናባችሁ እንዳማረ ተጀምሮ እንዳማረ የሚጠናቀቅ ሁነት...ሊሆን እንደማይችል ስታውቁት ልባችሁ ይወርድ የለ?እኔ ሁለመናዬ ነው የወረደው...ከእንጥሌ ጀምሮ... ልጁን በልቤ ረገምኩት...
'ከንፈርክን ስማ 'እንደ ወንድሜ ነው 'ማይህ ' ትበልህ'...'አልጋ አስይዛ ፔሬድ ላይ ነኝ ትበልህ!'... 'ፔሬዱ ሲሄድ 'ትንሽ ነው' ትበልህ' ብዬው ሳበቃ
"ቤቢ አሜን በል" አልኩት።
"አሜን"...ኤታባቱ!

እናም እኔ ወለተ ማርያም...የአብማይቱ ማርያም ልጅ...የማርቆሷ ሎጋ...ጠላታችሁን የሎስ ያክንፈውና አስተካክሎ 'ነገ' እንኳን ማለት ከማይችል ደቡቤ ጋር ከነፍኩ።ዘረኛ ነበርኩ...እልልልም ያልኩ ዘረኛ!ወንድ ጎጃሜ ካልሆነ ወንድ የማይመስለኝ!'ሲያናድደኝ የምሰድበው ስድብ እንኳን ካልገባው ምን ላደርገው ነው?' ብዬ የምራቀቂቱ...
''መቼ ይመችሃል?'' ስለው
"ነጌ"
"እንዴት አርገህ አበጃጀኸው?" ስለው
"እንደዚህ እንደዚህ 'አርግቼ' "
"እኔ ኦርቶዶክስ...አንተ ጴንጤ...በምን ስሌት አብረን እንሁን?"ስለው
" 'እምነት...ተስፋ...ፍቅር እነዚህ ሶስቱ ፀንተው ይኖራሉ፤ከሁሉም ግን ፍቅር ይበልጣል' ነው መፅሐፍ ቅዱስ 'የምለው' " ከሚለኝ አንድ ተላሰስ ጋር...ወደቅሁ።
መላመዳችን ሲበረታ...ቅርርባችን ልክ ሲያጣ ጥያቄዎቻችንን ሽሽት ገባን።መሄድ ብቻ!እስከሆነ ቀይ መስመር ድረስ...በድፍረት ጥያቄዎቻችንን ስር ድረስ የማንጠያየቀው የማይቀረውን መለያየት ያራቅን መስሎን ነበር።ጠንካራ አማኝም ባልሆን ፈሪ ነኝ...ነፍስ አባቴ ዘንድ ስከንፍ ሄጄ 'መናፍቅ ወድጄ ልቤ ጠፋ' አልኳቸው።
"ወለቴ"
"ኧይ አባ"
"እምን ድረስ ቀረብሽው?"
"ሲሉኝ?"
"ተመተቃቀፍ አለፋችሁ?" ሲሉኝ መሽኮርመም
"ወለቴ...አደራሽን አረከሰኝ እንዳትይኝ"
"ይፍቱኝ አባ"
"አዪዪዪዪዪ....አይ ወለቴ...ምነው?ህጉን ስታውቂው?" አሉኝ...የምፈታበት መፅሐፍ ተነበበ...ለሶስት ተከታታይ ቀናት ጠመቁኝ።
ህጉ 'ከአህዛብ አትጠጉ' ይላል...እንኳን አንሶላ መጋፈፍ...ማዕድ መካፈልን ያወግዛል...ግን ከህግ በላይ የሚገዛ፣ከውግዘት በላይ የሚያስር መሳሳብ ሲመጣስ?ምኔንም መሰሰት እስካልችል ከተሸነፍኩስ?አጅሬ አንዴ የሆነ መጣጥፍ ሲያነብልኝ "ሰው ከፍቅር የሚቆራረጠው ሰጥቶ መቀበልን ሲሻ ነው...የፍቅር ምክንያቱም ውጤቱም መስጠት ነው...ስለፍቅር የሚደረጉ ዝቅታዎች ሁሉ ከየትኛውም ከፍታ ይልቃሉ...ፍቅር ውስጥ መቀበልን የሚሻ እሱ ቀሽም ነው..." ብሎኝ ነበር።ያለስስት ስለሰጠሁት ሁሉ ደስተኛ ነኝ...አይደፈርን ደፍሬ፣አይተላለፉትን ተላልፌም...ይናፍቀኛል።
በስተ መጨረሻ...ተመርቆ ከጊቢ ሊወጣ ሳምንት ሲቀረው
"ተጠመቅና ከመሄድህ በፊት እንጋባ" ብዬ እስከምመረቅ ያሉትን ሶስት አመታት በዕምነት ልጠብቀው መዘጋጀቴን ነገርኩት...'ያዲያቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም' እንዲሉ
"አንቺ ወደኔ እንዳትመጪ ምንድነው 'ሚያግድሽ? ቤተሰብ ነው?''አለኝ።እርግጥ ነው ቤተሰቦቼ የሚያማልደውን እየሱስ እየመገቡ አላሳደጉኝም...ከነሱ በላይ ግን...ነጌ ምጤ ሲመጣ ማን ሊያዋልደኝ?ማን ጭንቄን ሊያረግብ?የሱ ቀበቶ በቂ አልነበረምና ልቤን ዳር እስከዳር እየከረሰሰኝ...ዘለዓለም የሚመስል ፅልመት እየወረሰኝ...ሸኘሁት...ማህተብ ፈቶ ቀለበት ማሰር የለም።

ዘማርቆስ
29/08/16

By @gize_yayeh

@wegoch
@wegoch
@paappii


>>Click here to continue<<

ወግ ብቻ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)


Fatal error: Uncaught TypeError: shuffle(): Argument #1 ($array) must be of type array, null given in /var/www/hottg/post.php:344 Stack trace: #0 /var/www/hottg/post.php(344): shuffle() #1 /var/www/hottg/route.php(63): include_once('...') #2 {main} thrown in /var/www/hottg/post.php on line 344