TG Telegram Group & Channel
ወግ ብቻ | United States America (US)
Create: Update:

ኒላ ዘ መንፈስ 4
(አሌክስ አብርሃም)

በክፍል ሶስት ትረካችን ኢትዮጵያዊቷ ፊደል እና በሂውማን ሄር ሰበብ በውስጧ የገባችው ኒላ የተባለች የሙት መንፈስ (የፀጉሩ ባለቤት ነኝ የምትል) ከብዙ ስድድብና አለመግባባት በኋላ ቀስ በቀስ እርስ በእርስ ማውራት እንደጀመሩ፤ ፊደል ነገሩ በቁጣና በሐይል የማይሆን ስለመሰላት በውስጧ ተቀምጣ እንደ አለቃ የምታዛትን ነጭናጫዋን ኒላን በፀባይ ለመያዝ እንደወሰነች አይተናል። ይባስ ብሎ ኒላ ገና በቀናት እድሜ ስለፊደልና መሰሎቿ ኢትዮጵያዊያን ባህሪ እየጠቀሰች ፊደልን መምከርና መውቀስ ጀምራለች! ቆሻሻ እንደማትወድ በመግለፅ የፊደልን ቤት አስፀድታታለች! ኒላ መንፈስ ናት፤ ከሁለት ዓመት በፊት ህንድ ውስጥ በ24 ዓመቷ በባቡር አደጋ የሞተች ሴት መንፈስ! ከሞቷ በፊት እጅግ የምትወደውና የምትሳሳለት ፀጉሯ «ሂውማን ሄር» ተብሎ ወደኢትዯጵያ ተላከ ! ፊደል የተባለች ታዋቂ ተዋናይት ገዝታ ተጠቀመችበት፤ በዛው ቅፅበት የኒላ መንፈስ በፀጉሩ በኩል የፊደልን ሰውነት ተጋርቶ መኖር ጀመረ! አሁን ፊደል ማለት አንዲት ሴት ግን በውስጧ ሁለተኛ መንፈስ የሚኖርባት ግራ የተጋባች ሴት ሆናለች! ቀጣዩን እነሆ!

* * ** *

«አንች ህንዳዊ ነሽ ፣ እንደነገርሽኝ ኢትዮጵያን ካወቅሻት ገና የተወሰኑ ቀናት ቢሆንሽ ነው! ግን ስለእኔም ይሁን ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልክ እዚህ ተወልዶ እንዳደገ ሰው ትናገሪያለሽ ! የምትይውን ነገር ሁሉ እንዴት አወቅሽው? » አለች ፊደል የኒላን ቁጣና ዘለፋ የተቀላቀለበት ምክር በዝምታ ስታዳምጥ ከቆየች በኋላ!

«ስለመንፈስ ምንም አታውቂም? ይሄ የሚበዛው ክፍሉ በማይረባ ዝባዝንኬ የተሞላ አዕምሮሽ ለእኔ እንደኮምፒውተር ወይም እንደስልክ ነው አሰራሩ! መንፈስ ሁኘ ውስጥሽ ስገባ ከህፃንነትሽ ጀምሮ እስከአሁን የተጠራቀመ ትዝታሽ ችሎታሽ ፣ባህሪሽ፣ ስሜትሽ ሁሉም ነገር አንች የምታውቂውና የምታስታውሸው ሁሉ እኔ «ሜሞሪ» ላይ ተጭኗል። ግን የምጠቀመው የምፈልገውን ሲሆን የምጠቀመውም በእኔ በራሴ መንገድ ብቻ ነው! የራሴ ህልውና አለኝ ፣የራሴ አስተሳሰብና ስሜት አለኝ፣ የራሴ ችሎታና አረዳድ አለኝ፣ የሌለኝ አካል ብቻ ነው!

አካሌ እዛ ህንድ ተቃጥሎ አመዱ ወንዝ ላይ ተበትኗል! ከእንግዲህ እነዛ ውብ የሰውነት ክፍሎቸ ዳግም አይመለሱም! ያ ውብ ፈገግታየ የለም ፣ ስለዚህ ፈገግታሽን እጋራለሁ፣ እነዛ ውብ እግሮቸ እና እጆቸ የሉም ስለዚህ የአንችን እግርና እጅ እጋራለሁ ፣ ከንፈሮቸ የሉም የአንችን ከንፈሮች እጋራለሁ. . . ለዛ ነው እንደአሳማ የሚያገሳና እንደውሻ የሚናከስ ትንፋሹ ጋን ጋን የሚሸት ወንድ እንዲስምሽ የማልፈልው! ሁለታችንም ያልተስማማንበት ወንድ አጠገብሽ አይደርስም! ምክንያቱም ሰውነትሽ ሰውነቴ ነው! ሂሂሂሂሂ ስንት ነገር አለ! የተረፈኝ ብቸኛ መታሰቢያ ይሄ አንች አናት ላይ የተቀመጠው ፀጉሬ ብቻ ነው! ይሄ ፀጉር ሁሉ ነገሬ ምድር ላይ የቀረኝ ብቸኛ መታሰቢያ ነው። ጓደኞቸ የምወዳቸው ቤተሰቦቸና ነፍሴን የምሰጥለት ፍቅረኛየ ሁሉም ተረት ናቸው አሁን!ለዘላለም አብረውኝ አይኖሩም! ህይዎት እንዴት አጭር ናት? " አለች ባዘነ ድምፅ!

«ፀጉርሽ እንዴት ተረፈ ግን?»

በቤተሰቦቸ እምነት ሴት ልጅ በህይዎት ዘመኗ ሁለት ጊዜ ፀጉሯን ለምናመልክበት ቤተ መቅደስ ትሰጣለች፣ ልክ እንደስዕለት ነው! አንድ ከማግባቷ በፊት፣ ትዳሯ እንዲባረክ (ይሄ በፍላጎት የሚደረግ ነው) ሁለተኛው በወጣትነቷ ከሞተች! እንደገና ስትፈጠር በመልካም ሰው ወይም እንስሳ እንድትፈጠር! እኔ ግን አንች ውስጥ ተፈጠርኩ ሂሂሂ!

ምናልባት ያኔ ፀጉሬን ስቆረጥ ቅር ስላለኝ አምላካችን አዝኖብኝ ይሆናል። ልክ እናተ አስራት መባ ስጦታ እንደምትሉት ነው! በበሃላችን ፀጉር የመጨረሻው የሴት ልጅ ክብር አንዲት ሴት ለምታመልከው ጣኦት ፀጉሯን መስጠቷ ክብሯን ኩራትና ፀጋዋን ሁሉ ለአምላኳ የመስጠት ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው! ወይም ከቸገራት ፀጉሯን ሸጣ ኑሮዋን ልትደጉም ትችላለች! ማንም ሴት ቸግሯት ፀጉሯን ስትሸጥ ደስ ብሏት አትሄድም ከእንባ ጋር ነው!

«ቤተመቅደሱ ፀጉሩ ምን ያደርግለታል?» አለች ፊደል

ቤተመቅደሱ ፀጉሩን ሰብስቦ ሂውማን ሄር ለሚያዘጋጁ ካምፓኒዎች ይሸጠዋል ! ካምፓኒዎቹ አዘጋጅተው ወደመላው ዓለም ይሸጡታል! የእኔም ፀጉር በዚሁ መንገድ ነው የሚመጣው! እኔ የመጀመሪያውን ፀጉሬን በሰጠሁበት ቀን ስድስት ሺ ሴቶች ሰጥተዋል። ወደሁለት ቶን ፀጉር ማለት ነው! ሁለት መቶ ኩንታል ማለት ነው! ይሄ አንዲት ትንሽ ከተማ ላይ ብቻ ነው፤ በመላው ህንድደግሞ ብዙ ሚሊየን ኩንታል ይሆናል! አሁን የገረመኝ ከዛ ሁሉ ጉድ ፀጉር ስንት አገር እያለ እንዲህ አይነት ከአመት አመት ፀሐይና አቧራ የማይለየው፣ ዜጎቹም ግራ የተጋቡበት አገር መንቃቴ ! ይባስ ብሎ እንደአንች አይነት በዚህ ዕድሜዋ እንደ 11 ዓመት ልጅ የምታስብ ሴት ውስጥ መኖሬ . . .» አለች። ፊደል ፈገግ አለችና

«ግንኮ በዕድሜ እበልጥሻለሁ ለምን አታከብሪኝም ኒላ?»

«እሱማ አገራችሁም በዕድሜ ስንቱን አገር ትቀድማለች ? ግን አሁንም ገና ትላንት እንደተመሰረተ አገር እንደተወዛገበች እንደተደናበረች ነው! ጉራ ብቻ! ገና ጡጦ ላይ እኮናችሁ! የሶስት ሽ ዓመት ሚሚ ! » ፊደል ዝም አለች! አገር ጅኒ ጃንካ ይደክማታል።

ፊደል ቀኑን ሙሉ ከተማ ወጥታ ልብስና አስቤዛ ስትገዛ ውላ ተመለሰች! ኒላ ልብስ ታመራርጣት ነበር። በአንዳንድ ምርጫቸው ስለማይጋቡ መጨቃጨቃቸው አልቀረም! ፊደልን ከሩቅ የሚያይዋት ሰዎች «ለየላት» ይላሉ! በተቻላት መጠን ዝም ለማለት ብትሞክርም የኒላ ጭቅጭቅ ዝም የሚኣስብል አልነበረም። እንደውም በአንድ ቀሚስ ከለር ምርጫ ስላልተግባቡ ወደቤት ሲመለሱ ተኮራርፈው ነበር።


ፊደል ሻዎር ወስዳ ራት በልታ ወደምኝታዋ ስትሄድ ኒላ ድንገት ወሬ ጀመረች «እኔ የምልሽ ፊደል . . .ለምን የፌስ ቡክ አካውንት አትከፍችም ?»
"አለኝ ምን ያደርግልኛል! "

ለአንች ማን አለሽ ?

እና ለማን ነው ?

ለእኔ !

እንዴ ጭራሽ ?

ምን ችግር አለው? በስሜ ክፈችልኝ ጓደኞቸን አገሬን ቤተሰቦቸን ማየት እፈልጋለሁ! የድሮ አካውንቴን ባስብ ባስብ ማስታወስ አልቻልኩም! ይመስለኛል የእኔን ሜሞሪ ፕሮሰስ የሚያደርገው የአንች አዕምሮ ማስታወስ ላይ ትንሽ ደከም ያለ ነው መሰል ሂሂሂ !

እና ፌስቡክ አካውንት ያለው መንፈስ ልትሆኝ? አለች ፊደል ነቆራዋን እንዳልሰማ አልፋ! በነገሩ ግርምት ተፈጥሮባት ነበር።

አዎ! ክፈችልኝ! በዛውም የፍቅረኛየን የእኔን የድሮ የጓደኞቸን ፎቶ አሳይሻለሁ!

ፊደል ጉጉትና ፍርሃት ተቀላቀለባት ! ግን ጉጉቷ አሸነፋት! ይች ከሁለት አመት በፊት ሞትኩ የምትል ሴት ምን ትመስል ይሆን? እውነት ናት አንደሰው ምድር ላይ ኑራ ነበር? ጓጓች ! «ከፈለግሽ ምን ቸገረኝ» አለችና ወደማንበቢያ ጠረጴዛዋ ሄደች! ውስጧ ግን የሆነ የጅል ስራ እንደምትሰራ እየነገራት ነበር። ላፕቶፗን ከፈተችና «እሽ በምን ስም ልክፈትልሽ? »

ኒላ N I L A ፊደል ስሙን አስገባች ! ድንገት ግን ኒላ በሳቅ ፍርስ አለች ! ሂሂሂሂሂ ሂሂሂሂሂሂ ካካካካካኣ

ምን ያስቅሻል?

ኒላ ዘ መንፈስ 4
(አሌክስ አብርሃም)

በክፍል ሶስት ትረካችን ኢትዮጵያዊቷ ፊደል እና በሂውማን ሄር ሰበብ በውስጧ የገባችው ኒላ የተባለች የሙት መንፈስ (የፀጉሩ ባለቤት ነኝ የምትል) ከብዙ ስድድብና አለመግባባት በኋላ ቀስ በቀስ እርስ በእርስ ማውራት እንደጀመሩ፤ ፊደል ነገሩ በቁጣና በሐይል የማይሆን ስለመሰላት በውስጧ ተቀምጣ እንደ አለቃ የምታዛትን ነጭናጫዋን ኒላን በፀባይ ለመያዝ እንደወሰነች አይተናል። ይባስ ብሎ ኒላ ገና በቀናት እድሜ ስለፊደልና መሰሎቿ ኢትዮጵያዊያን ባህሪ እየጠቀሰች ፊደልን መምከርና መውቀስ ጀምራለች! ቆሻሻ እንደማትወድ በመግለፅ የፊደልን ቤት አስፀድታታለች! ኒላ መንፈስ ናት፤ ከሁለት ዓመት በፊት ህንድ ውስጥ በ24 ዓመቷ በባቡር አደጋ የሞተች ሴት መንፈስ! ከሞቷ በፊት እጅግ የምትወደውና የምትሳሳለት ፀጉሯ «ሂውማን ሄር» ተብሎ ወደኢትዯጵያ ተላከ ! ፊደል የተባለች ታዋቂ ተዋናይት ገዝታ ተጠቀመችበት፤ በዛው ቅፅበት የኒላ መንፈስ በፀጉሩ በኩል የፊደልን ሰውነት ተጋርቶ መኖር ጀመረ! አሁን ፊደል ማለት አንዲት ሴት ግን በውስጧ ሁለተኛ መንፈስ የሚኖርባት ግራ የተጋባች ሴት ሆናለች! ቀጣዩን እነሆ!

* * ** *

«አንች ህንዳዊ ነሽ ፣ እንደነገርሽኝ ኢትዮጵያን ካወቅሻት ገና የተወሰኑ ቀናት ቢሆንሽ ነው! ግን ስለእኔም ይሁን ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልክ እዚህ ተወልዶ እንዳደገ ሰው ትናገሪያለሽ ! የምትይውን ነገር ሁሉ እንዴት አወቅሽው? » አለች ፊደል የኒላን ቁጣና ዘለፋ የተቀላቀለበት ምክር በዝምታ ስታዳምጥ ከቆየች በኋላ!

«ስለመንፈስ ምንም አታውቂም? ይሄ የሚበዛው ክፍሉ በማይረባ ዝባዝንኬ የተሞላ አዕምሮሽ ለእኔ እንደኮምፒውተር ወይም እንደስልክ ነው አሰራሩ! መንፈስ ሁኘ ውስጥሽ ስገባ ከህፃንነትሽ ጀምሮ እስከአሁን የተጠራቀመ ትዝታሽ ችሎታሽ ፣ባህሪሽ፣ ስሜትሽ ሁሉም ነገር አንች የምታውቂውና የምታስታውሸው ሁሉ እኔ «ሜሞሪ» ላይ ተጭኗል። ግን የምጠቀመው የምፈልገውን ሲሆን የምጠቀመውም በእኔ በራሴ መንገድ ብቻ ነው! የራሴ ህልውና አለኝ ፣የራሴ አስተሳሰብና ስሜት አለኝ፣ የራሴ ችሎታና አረዳድ አለኝ፣ የሌለኝ አካል ብቻ ነው!

አካሌ እዛ ህንድ ተቃጥሎ አመዱ ወንዝ ላይ ተበትኗል! ከእንግዲህ እነዛ ውብ የሰውነት ክፍሎቸ ዳግም አይመለሱም! ያ ውብ ፈገግታየ የለም ፣ ስለዚህ ፈገግታሽን እጋራለሁ፣ እነዛ ውብ እግሮቸ እና እጆቸ የሉም ስለዚህ የአንችን እግርና እጅ እጋራለሁ ፣ ከንፈሮቸ የሉም የአንችን ከንፈሮች እጋራለሁ. . . ለዛ ነው እንደአሳማ የሚያገሳና እንደውሻ የሚናከስ ትንፋሹ ጋን ጋን የሚሸት ወንድ እንዲስምሽ የማልፈልው! ሁለታችንም ያልተስማማንበት ወንድ አጠገብሽ አይደርስም! ምክንያቱም ሰውነትሽ ሰውነቴ ነው! ሂሂሂሂሂ ስንት ነገር አለ! የተረፈኝ ብቸኛ መታሰቢያ ይሄ አንች አናት ላይ የተቀመጠው ፀጉሬ ብቻ ነው! ይሄ ፀጉር ሁሉ ነገሬ ምድር ላይ የቀረኝ ብቸኛ መታሰቢያ ነው። ጓደኞቸ የምወዳቸው ቤተሰቦቸና ነፍሴን የምሰጥለት ፍቅረኛየ ሁሉም ተረት ናቸው አሁን!ለዘላለም አብረውኝ አይኖሩም! ህይዎት እንዴት አጭር ናት? " አለች ባዘነ ድምፅ!

«ፀጉርሽ እንዴት ተረፈ ግን?»

በቤተሰቦቸ እምነት ሴት ልጅ በህይዎት ዘመኗ ሁለት ጊዜ ፀጉሯን ለምናመልክበት ቤተ መቅደስ ትሰጣለች፣ ልክ እንደስዕለት ነው! አንድ ከማግባቷ በፊት፣ ትዳሯ እንዲባረክ (ይሄ በፍላጎት የሚደረግ ነው) ሁለተኛው በወጣትነቷ ከሞተች! እንደገና ስትፈጠር በመልካም ሰው ወይም እንስሳ እንድትፈጠር! እኔ ግን አንች ውስጥ ተፈጠርኩ ሂሂሂ!

ምናልባት ያኔ ፀጉሬን ስቆረጥ ቅር ስላለኝ አምላካችን አዝኖብኝ ይሆናል። ልክ እናተ አስራት መባ ስጦታ እንደምትሉት ነው! በበሃላችን ፀጉር የመጨረሻው የሴት ልጅ ክብር አንዲት ሴት ለምታመልከው ጣኦት ፀጉሯን መስጠቷ ክብሯን ኩራትና ፀጋዋን ሁሉ ለአምላኳ የመስጠት ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው! ወይም ከቸገራት ፀጉሯን ሸጣ ኑሮዋን ልትደጉም ትችላለች! ማንም ሴት ቸግሯት ፀጉሯን ስትሸጥ ደስ ብሏት አትሄድም ከእንባ ጋር ነው!

«ቤተመቅደሱ ፀጉሩ ምን ያደርግለታል?» አለች ፊደል

ቤተመቅደሱ ፀጉሩን ሰብስቦ ሂውማን ሄር ለሚያዘጋጁ ካምፓኒዎች ይሸጠዋል ! ካምፓኒዎቹ አዘጋጅተው ወደመላው ዓለም ይሸጡታል! የእኔም ፀጉር በዚሁ መንገድ ነው የሚመጣው! እኔ የመጀመሪያውን ፀጉሬን በሰጠሁበት ቀን ስድስት ሺ ሴቶች ሰጥተዋል። ወደሁለት ቶን ፀጉር ማለት ነው! ሁለት መቶ ኩንታል ማለት ነው! ይሄ አንዲት ትንሽ ከተማ ላይ ብቻ ነው፤ በመላው ህንድደግሞ ብዙ ሚሊየን ኩንታል ይሆናል! አሁን የገረመኝ ከዛ ሁሉ ጉድ ፀጉር ስንት አገር እያለ እንዲህ አይነት ከአመት አመት ፀሐይና አቧራ የማይለየው፣ ዜጎቹም ግራ የተጋቡበት አገር መንቃቴ ! ይባስ ብሎ እንደአንች አይነት በዚህ ዕድሜዋ እንደ 11 ዓመት ልጅ የምታስብ ሴት ውስጥ መኖሬ . . .» አለች። ፊደል ፈገግ አለችና

«ግንኮ በዕድሜ እበልጥሻለሁ ለምን አታከብሪኝም ኒላ?»

«እሱማ አገራችሁም በዕድሜ ስንቱን አገር ትቀድማለች ? ግን አሁንም ገና ትላንት እንደተመሰረተ አገር እንደተወዛገበች እንደተደናበረች ነው! ጉራ ብቻ! ገና ጡጦ ላይ እኮናችሁ! የሶስት ሽ ዓመት ሚሚ ! » ፊደል ዝም አለች! አገር ጅኒ ጃንካ ይደክማታል።

ፊደል ቀኑን ሙሉ ከተማ ወጥታ ልብስና አስቤዛ ስትገዛ ውላ ተመለሰች! ኒላ ልብስ ታመራርጣት ነበር። በአንዳንድ ምርጫቸው ስለማይጋቡ መጨቃጨቃቸው አልቀረም! ፊደልን ከሩቅ የሚያይዋት ሰዎች «ለየላት» ይላሉ! በተቻላት መጠን ዝም ለማለት ብትሞክርም የኒላ ጭቅጭቅ ዝም የሚኣስብል አልነበረም። እንደውም በአንድ ቀሚስ ከለር ምርጫ ስላልተግባቡ ወደቤት ሲመለሱ ተኮራርፈው ነበር።


ፊደል ሻዎር ወስዳ ራት በልታ ወደምኝታዋ ስትሄድ ኒላ ድንገት ወሬ ጀመረች «እኔ የምልሽ ፊደል . . .ለምን የፌስ ቡክ አካውንት አትከፍችም ?»
"አለኝ ምን ያደርግልኛል! "

ለአንች ማን አለሽ ?

እና ለማን ነው ?

ለእኔ !

እንዴ ጭራሽ ?

ምን ችግር አለው? በስሜ ክፈችልኝ ጓደኞቸን አገሬን ቤተሰቦቸን ማየት እፈልጋለሁ! የድሮ አካውንቴን ባስብ ባስብ ማስታወስ አልቻልኩም! ይመስለኛል የእኔን ሜሞሪ ፕሮሰስ የሚያደርገው የአንች አዕምሮ ማስታወስ ላይ ትንሽ ደከም ያለ ነው መሰል ሂሂሂ !

እና ፌስቡክ አካውንት ያለው መንፈስ ልትሆኝ? አለች ፊደል ነቆራዋን እንዳልሰማ አልፋ! በነገሩ ግርምት ተፈጥሮባት ነበር።

አዎ! ክፈችልኝ! በዛውም የፍቅረኛየን የእኔን የድሮ የጓደኞቸን ፎቶ አሳይሻለሁ!

ፊደል ጉጉትና ፍርሃት ተቀላቀለባት ! ግን ጉጉቷ አሸነፋት! ይች ከሁለት አመት በፊት ሞትኩ የምትል ሴት ምን ትመስል ይሆን? እውነት ናት አንደሰው ምድር ላይ ኑራ ነበር? ጓጓች ! «ከፈለግሽ ምን ቸገረኝ» አለችና ወደማንበቢያ ጠረጴዛዋ ሄደች! ውስጧ ግን የሆነ የጅል ስራ እንደምትሰራ እየነገራት ነበር። ላፕቶፗን ከፈተችና «እሽ በምን ስም ልክፈትልሽ? »

ኒላ N I L A ፊደል ስሙን አስገባች ! ድንገት ግን ኒላ በሳቅ ፍርስ አለች ! ሂሂሂሂሂ ሂሂሂሂሂሂ ካካካካካኣ

ምን ያስቅሻል?


>>Click here to continue<<

ወግ ብቻ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)