አንድ ወጣትና ሽማግሌ አይሁድ በባቡር ይጓዛሉ።
ወ፤ ስንት ሰዓት ነው?
ሽ፤ ዝም።
ወ፤ ይቅርታ ጌታዬ፣ ስንት ሰዓት ነው?
ሽ፤ ጭጭ።
ወ፤ ይቅርታ ጌታዬ እያናገርኩዎትኮ ነው፣ ለምንድነው የማይመልሱልኝ!! ስንት ሰዓት ሆኗል?
ሽ፤ ስማ አንት ጉብል። የሚቀጥለው ፌርማታ በዚህ መስመር የመጨረሻው ነው። አታውቀኝም አላውቅህም። ለሀገሩ እንግዳ ለሰዉ ባዳ ትመስላለህ። ለጥያቄህ መልስ ከሰጠሁ፣ ጨዋታ ልንጀምርና በዚያው ልንግባባ ነው። ስንወርድ "ወደቤት ጎራ በል" ማለቴ አይቀርም። እንደማይህ መልከመልካም ነህ፤ እኔ ደግሞ ቆንጆ ልጃገረድ ልጅ አለችኝ። ኋላ ፍቅር ውስጥ ትገቡና የመጋባት ፍላጎት ያድርባችኋል። እስቲ አንድ ነገር ንገረኝ፤ ምን ቆርጦኝ ነው የእጅ ሰዓት እንኳን መግዛት ለማይችል ሞሳ ልጄን የምድረው😊
By mengedenga
@wegoch
@wegoch
@paappii
>>Click here to continue<<