TG Telegram Group & Channel
አርማጌዶን | United States America (US)
Create: Update:

የነበረው የርዕዮተ ዓለም ትግል እንደነበር አውስተዋል።

በዓለም አቀፍም፣ በአኅጉርም ሆነ በኢትዮጵያ ደረጃ የነበረው የርዕዮተ ዓለም ትግል እንደነበረ ገልጸው፣ ይህ አካሄድ የቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃትን ተከትሎ ዓለም አቀፉን ትግል የሊበራሊዝም ወገን ካሻነፈ በኋላ፣ የመደብ ትግል ተቀዛቅዞ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን እየሆነ ያለው ማንነትን መሠረት ያደረገ (nationalism) ትግል ነው ብለዋል።

አቶ ተስፋለም፣ ‹‹በኢትዮጵያም እየታየ ያለው ከሐሳብ ወይም ከርዕዮተ ዓለም ይልቅ ማንነት መሠረት ያደረገ ትግል ነው ወይም ብሔርተኝነት ነው ጎልቶ እየወጣ ያለው። በአገሪቱ ውስጥ ኢትዮጵያዊ ማንነትን መሠረት ያደረግ ትግል ጠፍቷል የለም። ወደ ብሔር ወርዷል፤›› ሲሉ ተናግረዋል።

በማብራሪያቸው ድሮ ድሮ የመደብ ትግል ያገናኛቸው ነበር። ለላብ አደር፣ ለአርሶ አደር ወዘተ እየተባለ ሁሉንም ብሔር የሚያገናኝ፣ አብረው እንዲሠሩ የሚያደርግ የመደብ ትግል ነበር። ምሁራንም ይሁኑ ፖለቲካ ፓርቲዎች በእዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን ‹‹አሁን ግን ወደ ብሔርተኝነት ስለወረደ ሁሉም የየራሱን ወገን ይዞ፣ የትግራዩም ስለትግራይ ነው የሚታገለው፣ የኦሮሞውም ስለኦሮሞ ነው፣ ሌላውም እንደዚያው›› ሲሉ ገልጸውታል።

‹‹ከመንግሥት ጀምሮ አሁን ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ በሐሳብ አይደለም፣ ይህ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ሁንሉንም የሚያስማማ ሐሳብ የለውም። ወጥ የሆነ ትግል እንዳይካሄድ ያደረገው በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የኩነቶች ለውጥና በሀገሪቷ ያለው የፖለቲካ እሳቤ ያደረገው ሽግግር ነው›› ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

በምሁራን መካከል የውይይት አጀንዳ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል፣ ከ1966ዓ.ም አብዮት እስካሁን ድረስ ባሉት ዓመታት የተደረጉ የመንግሥታት ለውጦች ላይ ከተስተዋሉ ኩነቶች መካከል፣ በዋናነት ተጠቃሾቹ ሥልጣን የሚይዘው ኃይል አንድነታዊ ኃይል ሲሆን፣ የብሔርተኞች ተቃዋሚ ኃይል ሆኖ መገኘትና ብሔርተኛው ኃይል መንበር ሲይዝ ደግሞ የአንድነቱ በተቃርኖ የመቆም ጉዳይ ተጠቃሽ ናቸው።

ይህ ሁኔታ እንደዚህ ዓይነት የልዩነት ጫፎችን እንዴት ነው አስታርቆ መቀጠል የሚቻለው ወይስ ሌላ አማራጭ ሊበጅ ያስፈልጋል? የሚለውን ጥያቄ ፈጥሯል።

የሕግ ባለሙያው አቶ አንዷለም አሁን በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል በየትኛው ወገን ነው ያለው የሚለው ጉዳይ ግራ አጋቢ እንደሆነ ተናግረዋል።

‹‹እርግጥ ነው በብሔር የተደራጀ ኃይል ነው ሥልጣን የያዘው ምንም ጥያቄ የለውም። ነገር ግን በተመሳሳይ ጊዜ ፖለቲካዊ ርዕዮተ አለሙና ሊደርስበት የሚፈልገው ግብ አንጻር ግን በእርግጥም ብሔርተኛው ኃይል ነው ሥልጣን ላይ ያለው ብዬ ለመወሰን ይከብደኛል›› ብለዋል።

ለሐሳባቸው ማስረጃ ያቀረቡት ምክንያት፣ የሚፈልገው ኃይል ነው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ እንዳለ ሆኖ፣ ነገር ግን የአንድነት ኃይል የሚባለውንም ሥልጣን እንዲጋራው ማቅረቡን በመጥቀስ፣ የብሔርተኛ ኃይል ሥልጣን ይዞ የአንድነት ኃይል ተቃዋሚ ሆነ የሚለው ሁኔታ ላይ መገኘቱን ግን የሚያስረግጥ አካሄድ አይደለም ያለው ሲሉ ተናግረዋል።

‹‹በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት በርዕዮተ ዓለም ደረጃ ሲታሰብ የአንድነት ኃይል ነው የሚመስለው›› ብለው ‹‹ወረድ ሲባልና መሬት ላይ ያለው ሲታይ ደግሞ የጎሳ ፖለቲካ ከመቼውም ጊዜ በላይ የጨመረው አሁን ነው። እንደ ግብ ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥት እየሄደ ያለው ወደ ብሔርተኝነት ነው ብዬ አላምንም፤›› ሲሉ ተናግረዋል።

የአንድነት ኃይል መገለጫዎች ምንድናቸው የሚለው ጥያቄ ከሰንደቅ ዓላማም ይሁን ከቋንቋ አንፃር ወይም ሌላ ትክክለኛ መገለጫዎቹ ምንድናቸው የሚለው ጉዳይ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች በምሁራን መካከል ምላሽ የሚፈልግ ጉዳይ መሆኑም ተገልጿል።

በአሁን ወቅት ለሚታየው ለፖለቲካም ይሁን ለኢኮኖሚ ለውጥ የሚደረጉ ሰላማዊ ትግሎች መቀዛቀዝ ምንጭ ወሳኝ የሆነና በግልጽ የተቀመጠ ርዕዮተ ዓለም መታጣት ነው የሚሉ የክርክር መነሻ ሐሳቦች ከተለያዩ ወገኖች ይደመጣሉ።

እነዚህን ሐሳቦች የሚያነሱት አካላት በማስረጃነት የሚያቀርቡትም ለ66 ዓ.ም. አብዮት ሶሻሊዝምን እንደ ፍቱን አማራጭ አድርገው የያዙ ብዙኃን የነበሩት መሆኑን፣ የ83 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥም አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚለውን ይዞ መምጣቱን በመጥቀስ አሁን ላይ የሚደረጉ የፖለቲካ ትግሎች ግን ይህ ነው የሚባል ርዕዮተ ዓለም ሐሳብ ይዘው የሚነሱ አለመሆናቸውን ይጠቅሳሉ።

የሕግ ባለሙያው ይህ በግልጽ የሚታይ ክፍተት ነው ያሉ ሲሆን፣ በምሳሌነትም አሁን ያለው መንግሥት እየተመራበት ያለው ርዕዮተ ዓለም መደመር ነው ከተባለ፣ መደመር ርዕዮተ ዓለም ነው የሚለው ጉዳይ ግራ አጋቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ምክንያት አድርገው ያቀረቡትም፣ አንድ ርዕዮተ ዓለም አንድን አገር ለመምራት ደርሷል ተብሎ መታየት የሚችለው መጀመሪያ በእውቀት ደረጃ ተንሸራሽሮ፣ በከፍተኛ ትምህርት ቤቶች፣ በፀሐፊዎችና በሌሎችም ደረጃ በውይይት ዳብሮና ቀስ እያለ አድጎ ርዕዮት ዓለም ለመባል ሲበቃ ነው ብለዋል።

ሶሻሊዝምም ቢሆን በአንድ ጊዜ ርዕዮተ ዓለም ለመባል እንዳልበቃ፣ ይልቁንም የማርክስን የመነሻ ሐሳብ ይዞ በዓመታት ውስጥ ዳብሮ ተቀባይነት ለማግኘትና ለመተግበር ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው፣ በኢሕእዴግ ተግባራዊ የተደረገው አብዮታዊ ዴሞክራሲም ርዕዮተ ዓለምም ቢሆን በተለያዩ የዓለም አገሮች ተግባራዊ የተደረገ ርዕዮተ ዓለምን ለኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ይመጥናል ተብሎ በታሰበው መንገድ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለሕዝቡ እንደሚገባው መጠን ከርክመው ወደታች ያወረዱት ርዕዮተ ዓለም ነው በማለት አብራርተዋል።

የ66 ዓ.ም. አብዮትን በተመለከተ ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለትውልድ የተሸጋገሩ የአብዩቱ ትሩፋቶችና ዕዳዎች በተመለከተ በተደረገ ውይይት ላይ፣ የመሬት ጥያቄ አብዮቱን ካቀጠጣለው የመሬት ላራሹ ጥያቄ ተነስቶ አሁን ተመልሶ ገንዘብ ያላቸው ሰዎች መሬት እንዳሻቸው የሚሰበስቡበት ሁኔታ ላይ ደርሷል፡፡ እዚህ ላይ አስተያየታችሁ ምንድነው በሚል ከታዳሚዎች ለተነሳ ጥያቄ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽነር አቶ ዘገዬ አስፋው ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዘገዬ በቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በመሬት ይዞታ ሚኒስቴር ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን፣ የመሬት አዋጅ በሚወጣበት ጊዜ አዋጁን በማረም በኃላፊነት ተሳትፈዋል። የ1983 ዓ.ም. ለውጥ ተከትሎ በተቋቋመው የሽግግር መንግሥት የሕገ መንግሥት ማርቀቅ ሒደት ላይም ተሳትፈዋል።

የመሬት ጉዳይን በተመለከተ ላለፉት 50 ዓመታት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉት አቶ ዘገዬ፣ ከታዳሚ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በአሁን ወቅት ከመሬት ጋር ተያይዞ የተነሳው ሙሰኝነት በዚህ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን አገሪቷን ካጥለቀለቀው ሙሰኝነት ጋር የተያያዘ ነው ብለዋል።

በገጠር መሬት አዋጅ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ተብሎ የተደነገገው በአዋጁ መሠረት ራሱን እንደ ባለርስት ከሚቆጥረው አርሶ አደር ላይ ባለሀብት በማታለል መሬትን እንዳይሰበስብ ለማድረግ የተካተተ ነበር፡፡ ይህ ደግሞ አልተለወጠም ብለዋል።

ነገር ግን በመሬት ላይ ሙስና መስፋፋቱን ድርጊቱም በድብቅ ብቻ ሳይሆን በይፋ እየተደረገ የሚገኝ እየታየ የሚያስቆም ኃይል መጥፋቱ እንደሚያሳዝናቸው ገልጸዋል።

አቶ ዘገዬ ‹‹የመሬት ጉዳይ ላይ የሚታይ ሙስና በአጠቃላይ አሳሳቢና ማንም ደፍሮ የማይነካውም ስለሆነ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደፍሮ አንድ ትልቅ ውይይት የሚያካሂድበት ካልሆነ

የነበረው የርዕዮተ ዓለም ትግል እንደነበር አውስተዋል።

በዓለም አቀፍም፣ በአኅጉርም ሆነ በኢትዮጵያ ደረጃ የነበረው የርዕዮተ ዓለም ትግል እንደነበረ ገልጸው፣ ይህ አካሄድ የቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃትን ተከትሎ ዓለም አቀፉን ትግል የሊበራሊዝም ወገን ካሻነፈ በኋላ፣ የመደብ ትግል ተቀዛቅዞ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን እየሆነ ያለው ማንነትን መሠረት ያደረገ (nationalism) ትግል ነው ብለዋል።

አቶ ተስፋለም፣ ‹‹በኢትዮጵያም እየታየ ያለው ከሐሳብ ወይም ከርዕዮተ ዓለም ይልቅ ማንነት መሠረት ያደረገ ትግል ነው ወይም ብሔርተኝነት ነው ጎልቶ እየወጣ ያለው። በአገሪቱ ውስጥ ኢትዮጵያዊ ማንነትን መሠረት ያደረግ ትግል ጠፍቷል የለም። ወደ ብሔር ወርዷል፤›› ሲሉ ተናግረዋል።

በማብራሪያቸው ድሮ ድሮ የመደብ ትግል ያገናኛቸው ነበር። ለላብ አደር፣ ለአርሶ አደር ወዘተ እየተባለ ሁሉንም ብሔር የሚያገናኝ፣ አብረው እንዲሠሩ የሚያደርግ የመደብ ትግል ነበር። ምሁራንም ይሁኑ ፖለቲካ ፓርቲዎች በእዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን ‹‹አሁን ግን ወደ ብሔርተኝነት ስለወረደ ሁሉም የየራሱን ወገን ይዞ፣ የትግራዩም ስለትግራይ ነው የሚታገለው፣ የኦሮሞውም ስለኦሮሞ ነው፣ ሌላውም እንደዚያው›› ሲሉ ገልጸውታል።

‹‹ከመንግሥት ጀምሮ አሁን ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ በሐሳብ አይደለም፣ ይህ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ሁንሉንም የሚያስማማ ሐሳብ የለውም። ወጥ የሆነ ትግል እንዳይካሄድ ያደረገው በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የኩነቶች ለውጥና በሀገሪቷ ያለው የፖለቲካ እሳቤ ያደረገው ሽግግር ነው›› ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

በምሁራን መካከል የውይይት አጀንዳ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል፣ ከ1966ዓ.ም አብዮት እስካሁን ድረስ ባሉት ዓመታት የተደረጉ የመንግሥታት ለውጦች ላይ ከተስተዋሉ ኩነቶች መካከል፣ በዋናነት ተጠቃሾቹ ሥልጣን የሚይዘው ኃይል አንድነታዊ ኃይል ሲሆን፣ የብሔርተኞች ተቃዋሚ ኃይል ሆኖ መገኘትና ብሔርተኛው ኃይል መንበር ሲይዝ ደግሞ የአንድነቱ በተቃርኖ የመቆም ጉዳይ ተጠቃሽ ናቸው።

ይህ ሁኔታ እንደዚህ ዓይነት የልዩነት ጫፎችን እንዴት ነው አስታርቆ መቀጠል የሚቻለው ወይስ ሌላ አማራጭ ሊበጅ ያስፈልጋል? የሚለውን ጥያቄ ፈጥሯል።

የሕግ ባለሙያው አቶ አንዷለም አሁን በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል በየትኛው ወገን ነው ያለው የሚለው ጉዳይ ግራ አጋቢ እንደሆነ ተናግረዋል።

‹‹እርግጥ ነው በብሔር የተደራጀ ኃይል ነው ሥልጣን የያዘው ምንም ጥያቄ የለውም። ነገር ግን በተመሳሳይ ጊዜ ፖለቲካዊ ርዕዮተ አለሙና ሊደርስበት የሚፈልገው ግብ አንጻር ግን በእርግጥም ብሔርተኛው ኃይል ነው ሥልጣን ላይ ያለው ብዬ ለመወሰን ይከብደኛል›› ብለዋል።

ለሐሳባቸው ማስረጃ ያቀረቡት ምክንያት፣ የሚፈልገው ኃይል ነው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ እንዳለ ሆኖ፣ ነገር ግን የአንድነት ኃይል የሚባለውንም ሥልጣን እንዲጋራው ማቅረቡን በመጥቀስ፣ የብሔርተኛ ኃይል ሥልጣን ይዞ የአንድነት ኃይል ተቃዋሚ ሆነ የሚለው ሁኔታ ላይ መገኘቱን ግን የሚያስረግጥ አካሄድ አይደለም ያለው ሲሉ ተናግረዋል።

‹‹በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት በርዕዮተ ዓለም ደረጃ ሲታሰብ የአንድነት ኃይል ነው የሚመስለው›› ብለው ‹‹ወረድ ሲባልና መሬት ላይ ያለው ሲታይ ደግሞ የጎሳ ፖለቲካ ከመቼውም ጊዜ በላይ የጨመረው አሁን ነው። እንደ ግብ ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥት እየሄደ ያለው ወደ ብሔርተኝነት ነው ብዬ አላምንም፤›› ሲሉ ተናግረዋል።

የአንድነት ኃይል መገለጫዎች ምንድናቸው የሚለው ጥያቄ ከሰንደቅ ዓላማም ይሁን ከቋንቋ አንፃር ወይም ሌላ ትክክለኛ መገለጫዎቹ ምንድናቸው የሚለው ጉዳይ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች በምሁራን መካከል ምላሽ የሚፈልግ ጉዳይ መሆኑም ተገልጿል።

በአሁን ወቅት ለሚታየው ለፖለቲካም ይሁን ለኢኮኖሚ ለውጥ የሚደረጉ ሰላማዊ ትግሎች መቀዛቀዝ ምንጭ ወሳኝ የሆነና በግልጽ የተቀመጠ ርዕዮተ ዓለም መታጣት ነው የሚሉ የክርክር መነሻ ሐሳቦች ከተለያዩ ወገኖች ይደመጣሉ።

እነዚህን ሐሳቦች የሚያነሱት አካላት በማስረጃነት የሚያቀርቡትም ለ66 ዓ.ም. አብዮት ሶሻሊዝምን እንደ ፍቱን አማራጭ አድርገው የያዙ ብዙኃን የነበሩት መሆኑን፣ የ83 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥም አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚለውን ይዞ መምጣቱን በመጥቀስ አሁን ላይ የሚደረጉ የፖለቲካ ትግሎች ግን ይህ ነው የሚባል ርዕዮተ ዓለም ሐሳብ ይዘው የሚነሱ አለመሆናቸውን ይጠቅሳሉ።

የሕግ ባለሙያው ይህ በግልጽ የሚታይ ክፍተት ነው ያሉ ሲሆን፣ በምሳሌነትም አሁን ያለው መንግሥት እየተመራበት ያለው ርዕዮተ ዓለም መደመር ነው ከተባለ፣ መደመር ርዕዮተ ዓለም ነው የሚለው ጉዳይ ግራ አጋቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ምክንያት አድርገው ያቀረቡትም፣ አንድ ርዕዮተ ዓለም አንድን አገር ለመምራት ደርሷል ተብሎ መታየት የሚችለው መጀመሪያ በእውቀት ደረጃ ተንሸራሽሮ፣ በከፍተኛ ትምህርት ቤቶች፣ በፀሐፊዎችና በሌሎችም ደረጃ በውይይት ዳብሮና ቀስ እያለ አድጎ ርዕዮት ዓለም ለመባል ሲበቃ ነው ብለዋል።

ሶሻሊዝምም ቢሆን በአንድ ጊዜ ርዕዮተ ዓለም ለመባል እንዳልበቃ፣ ይልቁንም የማርክስን የመነሻ ሐሳብ ይዞ በዓመታት ውስጥ ዳብሮ ተቀባይነት ለማግኘትና ለመተግበር ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው፣ በኢሕእዴግ ተግባራዊ የተደረገው አብዮታዊ ዴሞክራሲም ርዕዮተ ዓለምም ቢሆን በተለያዩ የዓለም አገሮች ተግባራዊ የተደረገ ርዕዮተ ዓለምን ለኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ይመጥናል ተብሎ በታሰበው መንገድ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለሕዝቡ እንደሚገባው መጠን ከርክመው ወደታች ያወረዱት ርዕዮተ ዓለም ነው በማለት አብራርተዋል።

የ66 ዓ.ም. አብዮትን በተመለከተ ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለትውልድ የተሸጋገሩ የአብዩቱ ትሩፋቶችና ዕዳዎች በተመለከተ በተደረገ ውይይት ላይ፣ የመሬት ጥያቄ አብዮቱን ካቀጠጣለው የመሬት ላራሹ ጥያቄ ተነስቶ አሁን ተመልሶ ገንዘብ ያላቸው ሰዎች መሬት እንዳሻቸው የሚሰበስቡበት ሁኔታ ላይ ደርሷል፡፡ እዚህ ላይ አስተያየታችሁ ምንድነው በሚል ከታዳሚዎች ለተነሳ ጥያቄ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽነር አቶ ዘገዬ አስፋው ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዘገዬ በቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በመሬት ይዞታ ሚኒስቴር ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን፣ የመሬት አዋጅ በሚወጣበት ጊዜ አዋጁን በማረም በኃላፊነት ተሳትፈዋል። የ1983 ዓ.ም. ለውጥ ተከትሎ በተቋቋመው የሽግግር መንግሥት የሕገ መንግሥት ማርቀቅ ሒደት ላይም ተሳትፈዋል።

የመሬት ጉዳይን በተመለከተ ላለፉት 50 ዓመታት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉት አቶ ዘገዬ፣ ከታዳሚ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በአሁን ወቅት ከመሬት ጋር ተያይዞ የተነሳው ሙሰኝነት በዚህ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን አገሪቷን ካጥለቀለቀው ሙሰኝነት ጋር የተያያዘ ነው ብለዋል።

በገጠር መሬት አዋጅ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ተብሎ የተደነገገው በአዋጁ መሠረት ራሱን እንደ ባለርስት ከሚቆጥረው አርሶ አደር ላይ ባለሀብት በማታለል መሬትን እንዳይሰበስብ ለማድረግ የተካተተ ነበር፡፡ ይህ ደግሞ አልተለወጠም ብለዋል።

ነገር ግን በመሬት ላይ ሙስና መስፋፋቱን ድርጊቱም በድብቅ ብቻ ሳይሆን በይፋ እየተደረገ የሚገኝ እየታየ የሚያስቆም ኃይል መጥፋቱ እንደሚያሳዝናቸው ገልጸዋል።

አቶ ዘገዬ ‹‹የመሬት ጉዳይ ላይ የሚታይ ሙስና በአጠቃላይ አሳሳቢና ማንም ደፍሮ የማይነካውም ስለሆነ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደፍሮ አንድ ትልቅ ውይይት የሚያካሂድበት ካልሆነ


>>Click here to continue<<

አርማጌዶን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)