TG Telegram Group & Channel
አርማጌዶን | United States America (US)
Create: Update:

የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ሆነና እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ በአፍሪካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ መሆን አልቻልንም፡፡ የአፍሪካን አሥር በመቶ የሕዝብ ቁጥር መያዝ ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነ አገር ለአፍሪካዊ ጉዳዮች ባዳ ሆኖ የአፍሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ነፃነት ትግል ስኬት ላይ የሚፈጥረው ውስንነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡

አፍሪካዊ ማንነትን የተላበሰና በአፍሪካ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነቱን የሚወጣ የፖለቲካ ባህል የገነቡ አገሮች ገዥው ፓርቲም ይሁን የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይሁን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡ ደቡብ አፍሪካን ለአብነት እናንሳና ለአፍሪካ ቀን የሚሰጡትን ትኩረት በጨረፍታ እንመልከት፡፡

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) የአፍሪካ ቀንን በተለይዩ ፕሮግራሞች ያከብራል፡፡ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎችና ንግግር አቅራቢዎች ናቸው፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲ በኩልም ለምሳሌ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተርስ (EFF) የአፍሪካ ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል፡፡ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2022 የአፍሪካ ቀን ሲከበር የፓርቲው አባላት በመሪያቸው ጁሊየስ ማሌማ መሪነት በፈረንሣይ ኤምባሲ በመገኘት፣ ፈረንሣይ በቀድሞ የቅኝ ግዛቶቿ ላይ ያላትን ተፅዕኖ እንድታቆም የሚጠይቅና ጦሯን ከእነዚሁ የአፍሪካ አገሮች እንድታወጣ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ነበር፡፡ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማትም በኩል በተለይ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ ፋውንዴሽን የአፍሪካ ቀን ዓመታዊ ገለጻዎች (Annual Africa Day Lecture) ላለፉት 14 ዓመታት የተካሄደ ሲሆን፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ  እ.ኤ.አ. በ2019 በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተዘጋጀው የአፍሪካ ቀን ፕሮግራም ላይ ንግግር አቅራቢ እንደነበሩ እናስታውሳለን፡፡ የደቡብ አፍሪካን ልምድ ከአገራችን ጋር ማነፃፀሩን ብቻ ሳይሆን ምን እንማራለን የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ይሁን፡፡

ፖለቲካችን ከኢትዮጵያ ተሻግሮ አፍሪካዊ ማንነትን ወደተላበሰ ፖለቲካ ቢሸጋገር እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ ለአፍሪካችን የምናበረክተው አበርክቶ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአገራችን የሚኖረው በረከት ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከሰሞኑ በሌላ ጽሑፍ እመለስበታለሁ፡፡

ወደ ነጥቤ ስመለስ የትምህርት ሚኒስቴር በተለይም የሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ቁርጠኝነትና ተባባሪነትን በመመኘት ነው፡፡ የመጀመሪያው ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ 1209/2012 መሠረት የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ በትምህርት ቤቶች እንዲሰቀል፣ እንዲሁም መዝሙሩ እንዲዘመር የማድረግ ኃላፊነቱን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዲወጣ ነው፡፡ የአዋጁ መተግበር አፍሪካዊ ማንነቱን የሚያወድስ፣ በአፍሪካ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች የሚያይና ተግዳሮቶቿን በአሸናፊነት እንድትወጣ የድርሻውን መወጣት የሚችል ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡  

ሁለተኛው የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን አከባበር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ ኅብረት የ2024 መሪ ቃል ትምህርት ነው፡፡ ትምህርት የአኅጉራችን የትኩረት አቅጣጫ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች ከእስከ ዛሬው የተለየ ዝግጅቶች ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ወትሮውንም ትምህርት ቤቶች ዋና የአፍሪካ ቀን የድምቀት ቦታዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችን ከመዝናኛነት ባሻገር ምንም ዓይነት ታሪካዊም ሆነ ትምህርታዊ ፋይዳ የሌላቸው ‹‹ከለር ዴይ፣ ኦልዲስ ዴይ፣ ክሬዚ ዴይ…፣ ወዘተ›› እያከበሩ የአፍሪካ ቀን አለማክበራቸው አሳዛኝ ነው፡፡ ይህን ታሪክ ለመቀየር የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የትኩረት አቅጣጫው ትምህርት መሆኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የአፍሪካ ቀንን ማክበር እንዲጀምሩ ለማስቻል፣ ከዚህ የተሻለ ወቅትና ዕድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮዎች በኩል የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች እንዲከበር ጥሪ ቢያስተላልፍ ውጤቱ ለዘንድሮው የአፍሪካ ቀን በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ለመጪዎቹም ዓመታት ተማሪዎቹ የአፍሪካ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩና ስለአፍሪካ የተሻለ የማወቅ ዝንባሌ እንዲኖራቸው ያግዛል፡፡

አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካን ብዝኃነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ሙዚቃና ዳንስ ከተማሪዎች ጋር ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚያም ባሻገር ተማሪዎቹ ስለአፍሪካ ያላቸውን ዕውቀት የሚፈትሹበትና ለወደፊቱም ስለአፍሪካ የበለጠ ለማወቅ እንዲተጉ የሚያደርጉ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ ትብብሩን ካገኘን የአፍሪካ ቀን የትውልድ ቦታውን የሚመጥን የአፍሪካ ቀን አከባበር ይኖረናል፡፡ አፍሪካዊ ማንነታችንን እያወደስን የአፍሪካ ቀንን በጋራ እናክብር!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ

የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ሆነና እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ በአፍሪካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ መሆን አልቻልንም፡፡ የአፍሪካን አሥር በመቶ የሕዝብ ቁጥር መያዝ ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነ አገር ለአፍሪካዊ ጉዳዮች ባዳ ሆኖ የአፍሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ነፃነት ትግል ስኬት ላይ የሚፈጥረው ውስንነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡

አፍሪካዊ ማንነትን የተላበሰና በአፍሪካ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነቱን የሚወጣ የፖለቲካ ባህል የገነቡ አገሮች ገዥው ፓርቲም ይሁን የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይሁን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡ ደቡብ አፍሪካን ለአብነት እናንሳና ለአፍሪካ ቀን የሚሰጡትን ትኩረት በጨረፍታ እንመልከት፡፡

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) የአፍሪካ ቀንን በተለይዩ ፕሮግራሞች ያከብራል፡፡ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎችና ንግግር አቅራቢዎች ናቸው፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲ በኩልም ለምሳሌ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተርስ (EFF) የአፍሪካ ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል፡፡ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2022 የአፍሪካ ቀን ሲከበር የፓርቲው አባላት በመሪያቸው ጁሊየስ ማሌማ መሪነት በፈረንሣይ ኤምባሲ በመገኘት፣ ፈረንሣይ በቀድሞ የቅኝ ግዛቶቿ ላይ ያላትን ተፅዕኖ እንድታቆም የሚጠይቅና ጦሯን ከእነዚሁ የአፍሪካ አገሮች እንድታወጣ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ነበር፡፡ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማትም በኩል በተለይ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ ፋውንዴሽን የአፍሪካ ቀን ዓመታዊ ገለጻዎች (Annual Africa Day Lecture) ላለፉት 14 ዓመታት የተካሄደ ሲሆን፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ  እ.ኤ.አ. በ2019 በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተዘጋጀው የአፍሪካ ቀን ፕሮግራም ላይ ንግግር አቅራቢ እንደነበሩ እናስታውሳለን፡፡ የደቡብ አፍሪካን ልምድ ከአገራችን ጋር ማነፃፀሩን ብቻ ሳይሆን ምን እንማራለን የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ይሁን፡፡

ፖለቲካችን ከኢትዮጵያ ተሻግሮ አፍሪካዊ ማንነትን ወደተላበሰ ፖለቲካ ቢሸጋገር እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ ለአፍሪካችን የምናበረክተው አበርክቶ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአገራችን የሚኖረው በረከት ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከሰሞኑ በሌላ ጽሑፍ እመለስበታለሁ፡፡

ወደ ነጥቤ ስመለስ የትምህርት ሚኒስቴር በተለይም የሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ቁርጠኝነትና ተባባሪነትን በመመኘት ነው፡፡ የመጀመሪያው ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ 1209/2012 መሠረት የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ በትምህርት ቤቶች እንዲሰቀል፣ እንዲሁም መዝሙሩ እንዲዘመር የማድረግ ኃላፊነቱን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዲወጣ ነው፡፡ የአዋጁ መተግበር አፍሪካዊ ማንነቱን የሚያወድስ፣ በአፍሪካ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች የሚያይና ተግዳሮቶቿን በአሸናፊነት እንድትወጣ የድርሻውን መወጣት የሚችል ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡  

ሁለተኛው የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን አከባበር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ ኅብረት የ2024 መሪ ቃል ትምህርት ነው፡፡ ትምህርት የአኅጉራችን የትኩረት አቅጣጫ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች ከእስከ ዛሬው የተለየ ዝግጅቶች ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ወትሮውንም ትምህርት ቤቶች ዋና የአፍሪካ ቀን የድምቀት ቦታዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችን ከመዝናኛነት ባሻገር ምንም ዓይነት ታሪካዊም ሆነ ትምህርታዊ ፋይዳ የሌላቸው ‹‹ከለር ዴይ፣ ኦልዲስ ዴይ፣ ክሬዚ ዴይ…፣ ወዘተ›› እያከበሩ የአፍሪካ ቀን አለማክበራቸው አሳዛኝ ነው፡፡ ይህን ታሪክ ለመቀየር የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የትኩረት አቅጣጫው ትምህርት መሆኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የአፍሪካ ቀንን ማክበር እንዲጀምሩ ለማስቻል፣ ከዚህ የተሻለ ወቅትና ዕድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮዎች በኩል የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች እንዲከበር ጥሪ ቢያስተላልፍ ውጤቱ ለዘንድሮው የአፍሪካ ቀን በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ለመጪዎቹም ዓመታት ተማሪዎቹ የአፍሪካ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩና ስለአፍሪካ የተሻለ የማወቅ ዝንባሌ እንዲኖራቸው ያግዛል፡፡

አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካን ብዝኃነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ሙዚቃና ዳንስ ከተማሪዎች ጋር ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚያም ባሻገር ተማሪዎቹ ስለአፍሪካ ያላቸውን ዕውቀት የሚፈትሹበትና ለወደፊቱም ስለአፍሪካ የበለጠ ለማወቅ እንዲተጉ የሚያደርጉ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ ትብብሩን ካገኘን የአፍሪካ ቀን የትውልድ ቦታውን የሚመጥን የአፍሪካ ቀን አከባበር ይኖረናል፡፡ አፍሪካዊ ማንነታችንን እያወደስን የአፍሪካ ቀንን በጋራ እናክብር!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ


>>Click here to continue<<

አርማጌዶን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)