TG Telegram Group & Channel
አርማጌዶን | United States America (US)
Create: Update:

ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን

በአሮን ሰይፉ

የሰው ዘር መገኛ የሆነችውና የቀደምት ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው አፍሪካ በተለያዩ የታሪክ ዑደቶች ውስጥ ያለፈች አኅጉር ናት፡፡ በረዥሙ የአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላላቅ ሥልጣኔዎችን፣ የንግድ ልውውጦችን፣ የትምህርትና የባህል በረከቶቿ እንደሚነሳው ሁሉ በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣት አፍሪካውያንን ለባርነት አትላንቲክ ውቅያኖስን አቋርጠው ወደ አውሮፓና አሜሪካ መጫናቸው፣ እንዲሁም በአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት ሥር የመውደቅ ጨለማ ጊዜያትንም አሳልፋለች፡፡

እ.ኤ.አ. በ1884/85 በታሪክ የአፍሪካ ቅርምት ተብሎ በሚታወቀው የበርሊን ጉባዔ አውሮፓውያን አፍሪካን በቅኝ ለመያዝ ተከፋፈሉ፣ ኢትዮጵያ ዓድዋ ላይ ወራሪውን ጣልያንን ድል ነስታ፣ እንዲሁም ላይቤሪያ ከአሜሪካ ወደ አፍሪካ በተመለሱ ጥቁሮች የተመሠረተች አገር በመሆኗ ሁለቱ ብቻ ሲቀሩ መላ አፍሪካን አንድ በአንድ በቅኝ ግዛት መዳፋቸው ውስጥ አስገቡ፡፡ ይህ ወቅት አፍሪካ የራሷን ሥልጣኔና ነፃነት ያጣችበትና የአውሮፓውያን የጉልበትና የጥሬ ዕቃ ማግኛ ሥፍራ ብቻ እንድትሆን አድርጓል፡፡ የአፍሪካ ከራሷ ሐዲድ በመውጣት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮቿ የአውሮፓውያኑን ጥቅም በማማከል ይወሰን ስለነበር አፍሪካ በችግር አዙሪት ውስጥ እንድትዳክር አድርጓል፡፡

አፍሪካን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት መላ አፍሪካውያን እልህ አስጨራሽ ትግል አድርገዋል፡፡ ሚሊዮኖችም ለዚህ ቅዱስ ዓላማ ሕይወታቸውን ሰውተዋል፡፡ ከጋና እስከ ሱዳን፣ ከአልጄሪያ እስከ ናሚቢያ፣ ከኮንጎ እስከ ሞዛምቢክ  በአራቱም የአፍሪካ ማዕዘናት የተስፋፋው የነፃነት ትግል በጊዜ ሒደት ፍሬ እያፈራ በተለይ በ1950ዎቹና 60ዎቹ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል፡፡

አፍሪካውያን ነፃነታቸውን ማግኘት ሲጀምሩ የተፈጠረው መላ አፍሪካን ነፃ የማውጣት ተስፋና ጉጉት፣ ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች እየተሰባሰቡ እንዲመክሩ አስችሏል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካውያን መሰባሰብ አንድ ወጥ መሆን አልቻለም፡፡ የካዛብላንካ ቡድን በመባል የሚታወቀው አንደኛው ቡድን አፍሪካ አንድ አገር መሆን ይገባታል የሚል አቋም የነበረው ሲሆን፣ ሁለተኛውና የሞኖሮቪያ ቡድን የሚባለው የአፍሪካ አንድ አገርነት በሒደት የሚመጣ ሆኖ ነፃ አገሮቹ ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆምን የሚጠይቅ ነበር፡፡ የሁለቱ ቡድኖች አለመግባባት በቅኝ ግዛት ሥር እየማቀቁ ላሉ አፍሪካውያን ጥሩ ዜና አልነበረም፡፡

እ.ኤ.አ. በሜይ 1963 ይህ የአፍሪካ በሁለት ጎራ መሠለፍን ሊያስቀርና አፍሪካን በአንድ ድምፅ እንድትናገርና በአንድነት ለመቆም ማስቻልን ዓላማ ያደረገ ጉባዔ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ተካሄደ፡፡ የአፍሪካ ብሥራትም ተበሰረ፡፡ በሁለት ቡድኖች የተከፋፈሉት ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች በአንድነት በመቆም ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ያልቻሉትን አፍሪካውያን ነፃ ለማውጣት እ.ኤ.አ. ሜይ 25 ቀን 1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ይፋ አደረጉ፡፡ ይህች ታላቅ ቀን ‹‹የአፍሪካ ቀን›› በመባል በአፍሪካና በመላው ዓለም ለመታወቅ በቃች፡፡ ለዚህች ታሪካዊ ቀን ዕውን መሆን የኢትዮጵያ ሚና በእጅጉ የላቀ እንደነበር ዘለዓለም የሚዘከር ሆኖ፣ በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱት አቶ ከተማ ይፍሩ እ.ኤ.አ. በ1991 ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ‹‹አንድ ነገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አደረገች ብንል አንዱና ዋናው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መቋቋም ነው፤›› በማለት ገልጸውታል፡፡  

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና በመላው ዓለም ያለው አከባበር

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላቁ ቀን ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ከቅኝ ግዛት ቀንበር መላቀቅ ያቃታቸው አፍሪካውያን ባሉበት የተስፋ ዜናን የሰሙበት፣ የነፃነትን አየር የሚተነፍሱ አፍሪካውያንም በአንድነት ለአንድ ዓላማ መሠለፍን ያስቻለ ታላቅ ቀን ነው፡፡ አንድነቱም ተስፋ ብቻ ሆኖ አልቀረም፡፡ የነፃነት ትግሉን በማፋፋም መላ አፍሪካ ነፃ እንዲወጣ የዲፕሎማሲና ወታደራዊ ትግሉን አስተባብሮ ለድል እንዲበቃ አድርጓል፡፡ ይህ የታሪክ እውነታ ነው የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና ጥቁሮች በሚኖሩባቸው የዓለማችን ክፍሎች በደማቅ እንዲከበር ያደረገው፡፡

ደቡብ አፍሪካ የሜይ ወርን የአፍሪካ ወር የሚል ስያሜን የሰጠች ሲሆን፣ በወሩ ውስጥ የአፍሪካን ታሪክ፣ የነፃነት ትግልና ብሩህ ተስፋ፣ ወዘተ ይዳሰሳሉ፡፡ ይህም ሆኖ የአፍሪካ ቀን ብሔራዊ በዓል ሆኖ አልታወጀምና የአገሪቱ ዋና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆነው ጁሊየስ ማሌማ ፓርቲያቸው የአፍሪካ ቀንን ሲያከብር ለአባላቶቻቸው ባደረጉት ንግግር ይህን ብለዋል፡፡ ‹‹Africa Day is a celebration and recognition of Pan Africanism. We must not make a mistake comrades, and confuse this day to any other day. This day is a day when we celebrate our selves, this day is a day when we tell the whole world and those who care to listen that we are Africans and we are proud. …. But we must ask ourselves a question. Why is Africa Day not a public holiday in South Africa?››            

እንደ ዚምባቡዌ፣ ናሚቢያ፣ ማሊ፣ ዛምቢያ፣ ጋምቢያ፣ ሌሶቶ፣ ሞሪታኒያ ያሉ የአፍሪካ አገሮች የአፍሪካ ቀንን በብሔራዊ በዓልነት ያከብራሉ፡፡ ዋና መቀመጫውን በምሥረታ ቦታው ያደረገው የአፍሪካ ኅብረትም ሥራ ዝግ ሆኖ የሚከበር ቀን ነው፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ እንዲሁም በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች በተለያዩ የፌስቲቫልና የፓናል ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

ከአፍሪካ ውጭ ያሉ አገሮች የአፍሪካ ቀንን ከአፍሪካ ጋር ያላቸውን ትስስር የሚያጠናክሩበት መድረክ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡ በተለይ የሪፐብሊክ ኦፍ አየርላንድ የአፍሪካ ቀን አከባበር ከሌሎች አገሮችም በተሻለ የሚጠቀስ ነው፡፡ ለ2024 የአፍሪካ ቀን አከባበር በመንግሥት ድረ ገጽ ላይ ያለ ከወራት በፊት የተቀመጠው ማስታወቂያ እንዲህ ይላል፡፡

“Africa Day is returning this May – and set to be bigger and better than ever!

Events will be held in every county in Ireland to mark the day that celebrates Ireland’s growing links with the continent of Africa. Irish Aid is working with local authorities all over Ireland to plan a series of

ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን

በአሮን ሰይፉ

የሰው ዘር መገኛ የሆነችውና የቀደምት ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው አፍሪካ በተለያዩ የታሪክ ዑደቶች ውስጥ ያለፈች አኅጉር ናት፡፡ በረዥሙ የአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላላቅ ሥልጣኔዎችን፣ የንግድ ልውውጦችን፣ የትምህርትና የባህል በረከቶቿ እንደሚነሳው ሁሉ በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣት አፍሪካውያንን ለባርነት አትላንቲክ ውቅያኖስን አቋርጠው ወደ አውሮፓና አሜሪካ መጫናቸው፣ እንዲሁም በአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት ሥር የመውደቅ ጨለማ ጊዜያትንም አሳልፋለች፡፡

እ.ኤ.አ. በ1884/85 በታሪክ የአፍሪካ ቅርምት ተብሎ በሚታወቀው የበርሊን ጉባዔ አውሮፓውያን አፍሪካን በቅኝ ለመያዝ ተከፋፈሉ፣ ኢትዮጵያ ዓድዋ ላይ ወራሪውን ጣልያንን ድል ነስታ፣ እንዲሁም ላይቤሪያ ከአሜሪካ ወደ አፍሪካ በተመለሱ ጥቁሮች የተመሠረተች አገር በመሆኗ ሁለቱ ብቻ ሲቀሩ መላ አፍሪካን አንድ በአንድ በቅኝ ግዛት መዳፋቸው ውስጥ አስገቡ፡፡ ይህ ወቅት አፍሪካ የራሷን ሥልጣኔና ነፃነት ያጣችበትና የአውሮፓውያን የጉልበትና የጥሬ ዕቃ ማግኛ ሥፍራ ብቻ እንድትሆን አድርጓል፡፡ የአፍሪካ ከራሷ ሐዲድ በመውጣት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮቿ የአውሮፓውያኑን ጥቅም በማማከል ይወሰን ስለነበር አፍሪካ በችግር አዙሪት ውስጥ እንድትዳክር አድርጓል፡፡

አፍሪካን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት መላ አፍሪካውያን እልህ አስጨራሽ ትግል አድርገዋል፡፡ ሚሊዮኖችም ለዚህ ቅዱስ ዓላማ ሕይወታቸውን ሰውተዋል፡፡ ከጋና እስከ ሱዳን፣ ከአልጄሪያ እስከ ናሚቢያ፣ ከኮንጎ እስከ ሞዛምቢክ  በአራቱም የአፍሪካ ማዕዘናት የተስፋፋው የነፃነት ትግል በጊዜ ሒደት ፍሬ እያፈራ በተለይ በ1950ዎቹና 60ዎቹ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል፡፡

አፍሪካውያን ነፃነታቸውን ማግኘት ሲጀምሩ የተፈጠረው መላ አፍሪካን ነፃ የማውጣት ተስፋና ጉጉት፣ ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች እየተሰባሰቡ እንዲመክሩ አስችሏል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካውያን መሰባሰብ አንድ ወጥ መሆን አልቻለም፡፡ የካዛብላንካ ቡድን በመባል የሚታወቀው አንደኛው ቡድን አፍሪካ አንድ አገር መሆን ይገባታል የሚል አቋም የነበረው ሲሆን፣ ሁለተኛውና የሞኖሮቪያ ቡድን የሚባለው የአፍሪካ አንድ አገርነት በሒደት የሚመጣ ሆኖ ነፃ አገሮቹ ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆምን የሚጠይቅ ነበር፡፡ የሁለቱ ቡድኖች አለመግባባት በቅኝ ግዛት ሥር እየማቀቁ ላሉ አፍሪካውያን ጥሩ ዜና አልነበረም፡፡

እ.ኤ.አ. በሜይ 1963 ይህ የአፍሪካ በሁለት ጎራ መሠለፍን ሊያስቀርና አፍሪካን በአንድ ድምፅ እንድትናገርና በአንድነት ለመቆም ማስቻልን ዓላማ ያደረገ ጉባዔ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ተካሄደ፡፡ የአፍሪካ ብሥራትም ተበሰረ፡፡ በሁለት ቡድኖች የተከፋፈሉት ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች በአንድነት በመቆም ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ያልቻሉትን አፍሪካውያን ነፃ ለማውጣት እ.ኤ.አ. ሜይ 25 ቀን 1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ይፋ አደረጉ፡፡ ይህች ታላቅ ቀን ‹‹የአፍሪካ ቀን›› በመባል በአፍሪካና በመላው ዓለም ለመታወቅ በቃች፡፡ ለዚህች ታሪካዊ ቀን ዕውን መሆን የኢትዮጵያ ሚና በእጅጉ የላቀ እንደነበር ዘለዓለም የሚዘከር ሆኖ፣ በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱት አቶ ከተማ ይፍሩ እ.ኤ.አ. በ1991 ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ‹‹አንድ ነገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አደረገች ብንል አንዱና ዋናው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መቋቋም ነው፤›› በማለት ገልጸውታል፡፡  

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና በመላው ዓለም ያለው አከባበር

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላቁ ቀን ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ከቅኝ ግዛት ቀንበር መላቀቅ ያቃታቸው አፍሪካውያን ባሉበት የተስፋ ዜናን የሰሙበት፣ የነፃነትን አየር የሚተነፍሱ አፍሪካውያንም በአንድነት ለአንድ ዓላማ መሠለፍን ያስቻለ ታላቅ ቀን ነው፡፡ አንድነቱም ተስፋ ብቻ ሆኖ አልቀረም፡፡ የነፃነት ትግሉን በማፋፋም መላ አፍሪካ ነፃ እንዲወጣ የዲፕሎማሲና ወታደራዊ ትግሉን አስተባብሮ ለድል እንዲበቃ አድርጓል፡፡ ይህ የታሪክ እውነታ ነው የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና ጥቁሮች በሚኖሩባቸው የዓለማችን ክፍሎች በደማቅ እንዲከበር ያደረገው፡፡

ደቡብ አፍሪካ የሜይ ወርን የአፍሪካ ወር የሚል ስያሜን የሰጠች ሲሆን፣ በወሩ ውስጥ የአፍሪካን ታሪክ፣ የነፃነት ትግልና ብሩህ ተስፋ፣ ወዘተ ይዳሰሳሉ፡፡ ይህም ሆኖ የአፍሪካ ቀን ብሔራዊ በዓል ሆኖ አልታወጀምና የአገሪቱ ዋና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆነው ጁሊየስ ማሌማ ፓርቲያቸው የአፍሪካ ቀንን ሲያከብር ለአባላቶቻቸው ባደረጉት ንግግር ይህን ብለዋል፡፡ ‹‹Africa Day is a celebration and recognition of Pan Africanism. We must not make a mistake comrades, and confuse this day to any other day. This day is a day when we celebrate our selves, this day is a day when we tell the whole world and those who care to listen that we are Africans and we are proud. …. But we must ask ourselves a question. Why is Africa Day not a public holiday in South Africa?››            

እንደ ዚምባቡዌ፣ ናሚቢያ፣ ማሊ፣ ዛምቢያ፣ ጋምቢያ፣ ሌሶቶ፣ ሞሪታኒያ ያሉ የአፍሪካ አገሮች የአፍሪካ ቀንን በብሔራዊ በዓልነት ያከብራሉ፡፡ ዋና መቀመጫውን በምሥረታ ቦታው ያደረገው የአፍሪካ ኅብረትም ሥራ ዝግ ሆኖ የሚከበር ቀን ነው፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ እንዲሁም በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች በተለያዩ የፌስቲቫልና የፓናል ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

ከአፍሪካ ውጭ ያሉ አገሮች የአፍሪካ ቀንን ከአፍሪካ ጋር ያላቸውን ትስስር የሚያጠናክሩበት መድረክ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡ በተለይ የሪፐብሊክ ኦፍ አየርላንድ የአፍሪካ ቀን አከባበር ከሌሎች አገሮችም በተሻለ የሚጠቀስ ነው፡፡ ለ2024 የአፍሪካ ቀን አከባበር በመንግሥት ድረ ገጽ ላይ ያለ ከወራት በፊት የተቀመጠው ማስታወቂያ እንዲህ ይላል፡፡

“Africa Day is returning this May – and set to be bigger and better than ever!

Events will be held in every county in Ireland to mark the day that celebrates Ireland’s growing links with the continent of Africa. Irish Aid is working with local authorities all over Ireland to plan a series of


>>Click here to continue<<

አርማጌዶን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)