TG Telegram Group & Channel
አርማጌዶን | United States America (US)
Create: Update:

‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሕገወጥ መንገድና በሐሰተኛ ሰነድ አገር ውስጥ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት በመክሰስ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ሲሞከር፣ በዋስ እየተለቀቁ መቸገሩን አስታወቀ፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት የመኖሪያ ፈቃድ የጨረሱ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ሕጋዊ ዕርምጃ ከመውሰድ አንፃር ምን እየተሠራ እንደሆነ ከሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጥያቄ ቀርቦለታል፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የውጭ አገር ዜጎች ፈቃድ በተፈቀደላቸው የመኖሪያ የጊዜ ገደብ ብቻ እንዲቆዩ ከማድረግ አንፃር አፈጻጸሙ 36 በመቶ ብቻ መሆኑን በሪፖርቱ እንደተመለከተ በመግለጽ፣ በተቀመጠላቸው ጊዜ ማከናውን ለምን እንዳልተቻለ ጠይቋል፡፡

ተቋሙን እየመሩ ያሉት አመራሮች ወደ ኃላፊነት ሲመጡ ባደረጉት የዳሰሳ ጥናት፣ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎች ሐሰተኛ የመኖሪያ ፈቃድ እያዘጋጁ ሲጠቀሙና ሲሸጡ ቆይተዋል ሲሉ የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጎሳ ደምሴ ገልጸዋል፡፡

‹‹ይህ ሕገወጥ አሠራር ተለምዶ በመቆየቱ ዕርምጃ መወሰድ ሲጀመር በሁሉም አካላት እንደ አዲስና በመጥፎ ታይቷል፤›› ብለዋል፡፡ ተቋሙ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት ከሶ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ሲሞከርም፣ ‹‹አካልን ነፃ ማውጣት›› በሚል በዋስ እንዲለቀቁ እየተደረገ መቸገሩን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡ በዚህም በቀን የሚከፍሉትን ውዝፍ ገንዘብና ላጠፉት ጥፋት አስተዳደራዊ ቅጣት እየተቀጡ እንዲመለሱ ተደርጓል በማለት ገልጸዋል፡፡ 

በዚህ ወንጀል የተሳተፋ ዜጎችን የመለየት ሥራ የተከናወነውም ከደኅንነትና ከፀጥታ ተቋማት በተውጣጡ ጥምር የኮሚቴ አባላት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ 

ተቋሙ ከዚህ በፊት ተጠሪነቱ ለሰላም ሚኒስቴር መሆኑ ቀርቶ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆነ ራሱን የቻለ አደረጃት እንዲኖረው የሕግ ማሻሻያ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን፣ የሚሻሻለው ሕግ ሲፀድቅም አሁን ለሚነሱት ችግሮች መፍትሔ እንደሚያገኙ ጠቁመዋል፡፡  

ከዚህ ባለፈም ‹‹የአገሪቱ የቁጥጥር ሥርዓት ደካማ እንደሆነ ስለሚያውቁ›› በኢንቨስትመንት ስም ወደ አገር የገቡ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች አምስት ዓመትና ከዛ በላይ በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንም ገልጸዋል፡፡  

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ ባከናወነው የመስክ ምልከታ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ለእንግልት የሚዳርጉ አሠራሮችን መመልከቱን ገልጾ ማሻሻያ እንዲደረግበትና የሠራተኞች አያያዝ፣ ምቹ የሥራ ቦታን መፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ እንዲሠራ አሳስቧል፡፡

The post ‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ፅዮን ታደሰ

‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሕገወጥ መንገድና በሐሰተኛ ሰነድ አገር ውስጥ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት በመክሰስ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ሲሞከር፣ በዋስ እየተለቀቁ መቸገሩን አስታወቀ፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት የመኖሪያ ፈቃድ የጨረሱ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ሕጋዊ ዕርምጃ ከመውሰድ አንፃር ምን እየተሠራ እንደሆነ ከሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጥያቄ ቀርቦለታል፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የውጭ አገር ዜጎች ፈቃድ በተፈቀደላቸው የመኖሪያ የጊዜ ገደብ ብቻ እንዲቆዩ ከማድረግ አንፃር አፈጻጸሙ 36 በመቶ ብቻ መሆኑን በሪፖርቱ እንደተመለከተ በመግለጽ፣ በተቀመጠላቸው ጊዜ ማከናውን ለምን እንዳልተቻለ ጠይቋል፡፡

ተቋሙን እየመሩ ያሉት አመራሮች ወደ ኃላፊነት ሲመጡ ባደረጉት የዳሰሳ ጥናት፣ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎች ሐሰተኛ የመኖሪያ ፈቃድ እያዘጋጁ ሲጠቀሙና ሲሸጡ ቆይተዋል ሲሉ የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጎሳ ደምሴ ገልጸዋል፡፡

‹‹ይህ ሕገወጥ አሠራር ተለምዶ በመቆየቱ ዕርምጃ መወሰድ ሲጀመር በሁሉም አካላት እንደ አዲስና በመጥፎ ታይቷል፤›› ብለዋል፡፡ ተቋሙ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት ከሶ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ሲሞከርም፣ ‹‹አካልን ነፃ ማውጣት›› በሚል በዋስ እንዲለቀቁ እየተደረገ መቸገሩን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡ በዚህም በቀን የሚከፍሉትን ውዝፍ ገንዘብና ላጠፉት ጥፋት አስተዳደራዊ ቅጣት እየተቀጡ እንዲመለሱ ተደርጓል በማለት ገልጸዋል፡፡ 

በዚህ ወንጀል የተሳተፋ ዜጎችን የመለየት ሥራ የተከናወነውም ከደኅንነትና ከፀጥታ ተቋማት በተውጣጡ ጥምር የኮሚቴ አባላት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ 

ተቋሙ ከዚህ በፊት ተጠሪነቱ ለሰላም ሚኒስቴር መሆኑ ቀርቶ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆነ ራሱን የቻለ አደረጃት እንዲኖረው የሕግ ማሻሻያ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን፣ የሚሻሻለው ሕግ ሲፀድቅም አሁን ለሚነሱት ችግሮች መፍትሔ እንደሚያገኙ ጠቁመዋል፡፡  

ከዚህ ባለፈም ‹‹የአገሪቱ የቁጥጥር ሥርዓት ደካማ እንደሆነ ስለሚያውቁ›› በኢንቨስትመንት ስም ወደ አገር የገቡ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች አምስት ዓመትና ከዛ በላይ በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንም ገልጸዋል፡፡  

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ ባከናወነው የመስክ ምልከታ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ለእንግልት የሚዳርጉ አሠራሮችን መመልከቱን ገልጾ ማሻሻያ እንዲደረግበትና የሠራተኞች አያያዝ፣ ምቹ የሥራ ቦታን መፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ እንዲሠራ አሳስቧል፡፡

The post ‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ፅዮን ታደሰ


>>Click here to continue<<

አርማጌዶን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)