ይህ እርግዝና እና ወሊድ የተሰኘው መፅሐፍ ከጦቢት የህክምና መጻሕፍት የመጀመሪያው ሲሆን በ10 አንቀጾች የተከተበ ባለ 90 ገፅ ጽሁፍ ነው፡፡ መፅሀፉ እንደ መንደርደሪያ የሴት መራቢያ አካላት መዋቅርንና የወርአበባ ዑደትን ካነሳ በኋላ የፅንስ መፈጠር ሂደትን ከእንቁላል እና የዘር ፍሬ መዋሐድ አንስቶ እስከ ውልደት ድረስ ያሉ ዋና ዋና ነጥቦችን ያስቀምጣል፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ ግር ያለ ግንዛቤ ያለባቸውን የእንግዴ ልጅ፣ የሽርት ውሃ፣ እትብት እና የመሳሰሉትን በማብራራት በተወሰነ መልኩ በእነዚህ የአካል ክፍላት ላይ ሊኖሩ ስለሚችሉ መዛባቶች እና የሕክምና ሂደቶች ግንዛቤ የሚሰጥ ክፍልንም የያዘ ነው፡፡ በእርግዝና ጊዜ በነፍሰጡሯ ሊወሰዱ የሚችሉ እነ አልኮል፣ ሲጋራ እና ሌሎች መድኃኒቶች ምን ጉዳት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ፣ እንዲሁም ሾተላይ በመባል የሚጠራው ክስተት አፈጣጠር እና ጉዳት በፅሁፉ ውስጥ የተካተቱ ሌሎች ነገሮች ሲሆኑ ስለቅድመ ወሊድ ክትትል እና ስለምጥ እና ወሊድ ሂደት ደግሞ በመጨረሻዎቹ ምዕራፎች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡
መፅሀፉ በሕክምና ባለሙያዎች እና በነፍሰጡር ሴቶች መካከል ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለማጥበብ የሚሞክር እና በማህጸን ውስጥ ቆይታ ምን እንደሚፈጠር ለማወቅ ለሚጓጉ አንባቢያን ሁሉ ጥማቸውን የሚያረኩበት፣ ለመረዳት የማያስቸግር እጥር ምጥን ያለ ጽሁፍ ነው!! @berana book store 5kilo Infront of kidiste mariam, & Ezop book store piassa... Coming soon at other stores & cities
>>Click here to continue<<