TG Telegram Group & Channel
Tiriyachen | ጥሪያችን | United States America (US)
Create: Update:

መላእክት እንዴት ዐወቁ?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

49፥18 *”አላህ የሰማያትን እና የምድርን ሩቅ ሚስጥር ያውቃል”*። إِنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ غَيْبَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ

“አል-ገይብ” ٱلْغَيْب ማለት “የሩቅ ሚስጥር” ማለት ሲሆን ከሩቅ ሚስጥራት መካከል “አል-ገይቡል ሙሥተቅበል” ٱلْغَيْب ٱلْمُسْتَقْبَل ማለት “መጻእያት የሩቅ ሚስጥር” ነው፦
49፥18 *”አላህ የሰማያትን እና የምድርን ሩቅ ሚስጥር ያውቃል”*። إِنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ غَيْبَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ

ሰው ከመፈጠሩ በፊት ምን እንደሚያደርግ አላህ ቀድሞውኑ ያውቀዋል። ሰው ከሚያደርጋቸው መካከል በምድር ውስጥ ማጥፋት እና ደም ማፍሰስ ነው፦
26፥152 *«የእነዚያን በምድር ውስጥ የሚያጠፉትን እና የማያበጁትን፡፡»* الَّذِينَ يُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ وَلَا يُصْلِحُونَ
2፥84 *"ደሞቻችሁን አታፍስሱ ነፍሶቻችሁንም ከፊላችሁን ከአገሮቻችሁ አታውጡ የምንል ስንኾን የጠበቀ ቃል ኪዳናችሁን በያዝንባችሁ ጊዜ አስታውሱ"*፡፡ وَإِذْ أَخَذْنَا مِيثَاقَكُمْ لَا تَسْفِكُونَ دِمَاءَكُمْ وَلَا تُخْرِجُونَ أَنفُسَكُم مِّن دِيَارِكُمْ

ሰው በምድር ውስጥ እንደሚያጠፋ እና ደም እንደሚያፈስ ከመፈጠሩ በፊት መላእክት ያውቁ ነበር፦
2፥30 *ጌታህ ለመላእክት፡- «እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ፤» ባለ ጊዜ የኾነውን አስታውስ። እነርሱም «እኛ ከማመስገን ጋር የምናጠራህ፥ ለአንተም የምንቀድስ ስንኾን በእርሷ ውስጥ የሚያጠፋን እና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን?» አሉ፡፡ አላህም «እኔ የማታውቁትን ነገር አውቃለሁ» አላቸው*፡፡ وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي جَاعِلٌ فِي الْأَرْضِ خَلِيفَةً ۖ قَالُوا أَتَجْعَلُ فِيهَا مَن يُفْسِدُ فِيهَا وَيَسْفِكُ الدِّمَاءَ وَنَحْنُ نُسَبِّحُ بِحَمْدِكَ وَنُقَدِّسُ لَكَ ۖ قَالَ إِنِّي أَعْلَمُ مَا لَا تَعْلَمُون

አላህ ለመላእክት፡- "እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ" ሲል፥ እነርሱም፦ "በእርሷ ውስጥ የሚያጠፋን እና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን? አሉት። ይህንን እንዴት ዐወቁ? ለሚለው ጥያቄ መልሱ አላህ ዐሳውቋቸው ነው፦
2፥32 *«ጥራት ይገባህ፤ ካሳወከን ነገር በስተቀር ለእኛ ዕውቀት የለንም፡፡ አንተ ዐዋቂው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና» አሉ*፡፡ قَالُوا سُبْحَانَكَ لَا عِلْمَ لَنَا إِلَّا مَا عَلَّمْتَنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ الْعَلِيمُ الْحَكِيمُ

"ካሳወከን ነገር በስተቀር ለእኛ ዕውቀት የለንም" ካሉ አላህ ካሳወቃቸው ውጪ በራሳቸው ዕውቀት ከሌላቸው ሰው በምድር ውስጥ እንደሚያጠፋ እና ደም እንደሚያፈስ ከመፈጠሩ በፊት አላህ ዐሳውቋቸዋል። እንዲገባችሁ ከባይብል ሁለት ጥቅሶችን እንመልከት፦
ዘፍጥረት 16፥11-12 *"የእግዚአብሔር መልአክም አላት፦ እነሆ አንቺ ፀንሰሻል፥ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም እስማኤል ብለሽ ትጠሪዋለሽ፥ እግዚአብሔር መቸገርሽን ሰምቶአልና። እርሱም የበዳ አህያን የሚመስል ሰው ይሆናል፥ እጁ በሁሉ ላይ ይሆናል፥ የሁሉም እጅ ደግሞ በእርሱ ላይ ይሆናል፤ እርሱም በወንድሞቹ ሁሉ ፊት ይኖራል*።

መልአኩ እስማኤል ከመፀነሱ በፊት መልአኩ አጋር እንደምትፀንስ፥ ወንድ ልጅንም እንደምትወልድ፤ ስሙንም እስማኤል ብላ እንደምትጠራው። እስማኤል የበዳ አህያን የሚመስል ሰው እንደሚሆን፥ እጁ በሁሉ ላይ እንደሚሆን፥ የሁሉም እጅ ደግሞ በእርሱ ላይ እንደሚሆን፤ እርሱም በወንድሞቹ ሁሉ ፊት እንደሚኖር በምን ዐወቀ? እንዴ! "እግዚአብሔር ለመልአኩ ቀድሞውኑ ዐሳውቋቸው እንጂ መላእክት የቀደመ ዕውቀት በራሳቸው የላቸውም" ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም እሳቤ በዚህ ስሌት መረዳት ይቻላል፦
መሣፍንት 13፥5 *እነሆ ትፀንሻለሽ፥ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናልና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ እርሱም እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን ይጀምራል*።

መልአኩ ሳምሶን ከመፀነሱ በፊት መልአኩ የማኑሄ ሚስት እንደምትፀንስ፥ ወንድ ልጅንም እንደምትወልድ። ሳምሶን ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ እንደሚሆን፥ በራሱ ላይ ምላጭ እንደማይደርስበት። ሳምሶን እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን እንደሚጀምር በምን ዐወቀ? እንዴ! "እግዚአብሔር ለመልአኩ ቀድሞውኑ ዐሳውቋቸው እንጂ መላእክት የቀደመ ዕውቀት በራሳቸው የላቸውም" ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም እሳቤ በዚህ ሒሳብ መረዳት ይቻላል። ተግባባን አይደል? አዎ! ግን ለመላእክትን ቀድሞ መናገሩ ለምን አስፈለገ? ይህ የአላህ ምርጫ ነው። እሩቅ ሳንሄድ እግዚአብሔር ምሥጢሩን ለባሪያዎቹ ለነቢያት ካልነገረ በቀር ምንም አያደርግም፦
አሞጽ 3፥7 *"በእውነት ጌታ እግዚአብሔር ምሥጢሩን ለባሪያዎቹ ለነቢያት ካልነገረ በቀር ምንም አያደርግም"*።

እግዚአብሔር ምንም ነገር ከማድረጉ በፊት ለነቢያቱ መናገሩ ችግር ከሌለው አላህ ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ሰውን እንደሚፈጥር ለመላእክት መናገሩ ችግር የለውም። ምነው እግዚአብሔር ሰውን ከመፈጠሩ በፊት ለመላእክት "እንፍጠር" ብሏቸው የለ እንዴ? የባሰ ጉድ፦
ኩፋሌ 4፥4 *ፈጣሪያችን* እግዚአብሔር ለእኛ *እንዲህ አለን*፦ “ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *”እንፍጠርለት”*።

“ፈጣሪያችን” የሚል ሃይለ-ቃል ይሰመርበት። "ፈጣሪያችን" ለእኛ "እንፍጠርለት" አለን እያለ ለሙሴ የሚተርክለት አንድ መልአክ ነው፦
ኩፋሌ 2፥4 *የፊቱ መልአክ በእግዚአብሔር ቃል ታዞ ሙሴን እንዲህ አለው*፦

በማለት እግዚአብሔር ለመላእክት እንፍጠርለት እንዳለ ይህ የኩፋሌ መጽሐፍ ይናገራል። የምጣዱ እያለ የዕንቅቡ ተንጣጣ። ቅቤ አንጣሪዋ እያለች ጎመን ቀንጣሿን ምች መታት።

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen
ወሠላሙ ዐለይኩም

መላእክት እንዴት ዐወቁ?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

49፥18 *”አላህ የሰማያትን እና የምድርን ሩቅ ሚስጥር ያውቃል”*። إِنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ غَيْبَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ

“አል-ገይብ” ٱلْغَيْب ማለት “የሩቅ ሚስጥር” ማለት ሲሆን ከሩቅ ሚስጥራት መካከል “አል-ገይቡል ሙሥተቅበል” ٱلْغَيْب ٱلْمُسْتَقْبَل ማለት “መጻእያት የሩቅ ሚስጥር” ነው፦
49፥18 *”አላህ የሰማያትን እና የምድርን ሩቅ ሚስጥር ያውቃል”*። إِنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ غَيْبَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ

ሰው ከመፈጠሩ በፊት ምን እንደሚያደርግ አላህ ቀድሞውኑ ያውቀዋል። ሰው ከሚያደርጋቸው መካከል በምድር ውስጥ ማጥፋት እና ደም ማፍሰስ ነው፦
26፥152 *«የእነዚያን በምድር ውስጥ የሚያጠፉትን እና የማያበጁትን፡፡»* الَّذِينَ يُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ وَلَا يُصْلِحُونَ
2፥84 *"ደሞቻችሁን አታፍስሱ ነፍሶቻችሁንም ከፊላችሁን ከአገሮቻችሁ አታውጡ የምንል ስንኾን የጠበቀ ቃል ኪዳናችሁን በያዝንባችሁ ጊዜ አስታውሱ"*፡፡ وَإِذْ أَخَذْنَا مِيثَاقَكُمْ لَا تَسْفِكُونَ دِمَاءَكُمْ وَلَا تُخْرِجُونَ أَنفُسَكُم مِّن دِيَارِكُمْ

ሰው በምድር ውስጥ እንደሚያጠፋ እና ደም እንደሚያፈስ ከመፈጠሩ በፊት መላእክት ያውቁ ነበር፦
2፥30 *ጌታህ ለመላእክት፡- «እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ፤» ባለ ጊዜ የኾነውን አስታውስ። እነርሱም «እኛ ከማመስገን ጋር የምናጠራህ፥ ለአንተም የምንቀድስ ስንኾን በእርሷ ውስጥ የሚያጠፋን እና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን?» አሉ፡፡ አላህም «እኔ የማታውቁትን ነገር አውቃለሁ» አላቸው*፡፡ وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي جَاعِلٌ فِي الْأَرْضِ خَلِيفَةً ۖ قَالُوا أَتَجْعَلُ فِيهَا مَن يُفْسِدُ فِيهَا وَيَسْفِكُ الدِّمَاءَ وَنَحْنُ نُسَبِّحُ بِحَمْدِكَ وَنُقَدِّسُ لَكَ ۖ قَالَ إِنِّي أَعْلَمُ مَا لَا تَعْلَمُون

አላህ ለመላእክት፡- "እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ" ሲል፥ እነርሱም፦ "በእርሷ ውስጥ የሚያጠፋን እና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን? አሉት። ይህንን እንዴት ዐወቁ? ለሚለው ጥያቄ መልሱ አላህ ዐሳውቋቸው ነው፦
2፥32 *«ጥራት ይገባህ፤ ካሳወከን ነገር በስተቀር ለእኛ ዕውቀት የለንም፡፡ አንተ ዐዋቂው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና» አሉ*፡፡ قَالُوا سُبْحَانَكَ لَا عِلْمَ لَنَا إِلَّا مَا عَلَّمْتَنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ الْعَلِيمُ الْحَكِيمُ

"ካሳወከን ነገር በስተቀር ለእኛ ዕውቀት የለንም" ካሉ አላህ ካሳወቃቸው ውጪ በራሳቸው ዕውቀት ከሌላቸው ሰው በምድር ውስጥ እንደሚያጠፋ እና ደም እንደሚያፈስ ከመፈጠሩ በፊት አላህ ዐሳውቋቸዋል። እንዲገባችሁ ከባይብል ሁለት ጥቅሶችን እንመልከት፦
ዘፍጥረት 16፥11-12 *"የእግዚአብሔር መልአክም አላት፦ እነሆ አንቺ ፀንሰሻል፥ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም እስማኤል ብለሽ ትጠሪዋለሽ፥ እግዚአብሔር መቸገርሽን ሰምቶአልና። እርሱም የበዳ አህያን የሚመስል ሰው ይሆናል፥ እጁ በሁሉ ላይ ይሆናል፥ የሁሉም እጅ ደግሞ በእርሱ ላይ ይሆናል፤ እርሱም በወንድሞቹ ሁሉ ፊት ይኖራል*።

መልአኩ እስማኤል ከመፀነሱ በፊት መልአኩ አጋር እንደምትፀንስ፥ ወንድ ልጅንም እንደምትወልድ፤ ስሙንም እስማኤል ብላ እንደምትጠራው። እስማኤል የበዳ አህያን የሚመስል ሰው እንደሚሆን፥ እጁ በሁሉ ላይ እንደሚሆን፥ የሁሉም እጅ ደግሞ በእርሱ ላይ እንደሚሆን፤ እርሱም በወንድሞቹ ሁሉ ፊት እንደሚኖር በምን ዐወቀ? እንዴ! "እግዚአብሔር ለመልአኩ ቀድሞውኑ ዐሳውቋቸው እንጂ መላእክት የቀደመ ዕውቀት በራሳቸው የላቸውም" ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም እሳቤ በዚህ ስሌት መረዳት ይቻላል፦
መሣፍንት 13፥5 *እነሆ ትፀንሻለሽ፥ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናልና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ እርሱም እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን ይጀምራል*።

መልአኩ ሳምሶን ከመፀነሱ በፊት መልአኩ የማኑሄ ሚስት እንደምትፀንስ፥ ወንድ ልጅንም እንደምትወልድ። ሳምሶን ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ እንደሚሆን፥ በራሱ ላይ ምላጭ እንደማይደርስበት። ሳምሶን እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን እንደሚጀምር በምን ዐወቀ? እንዴ! "እግዚአብሔር ለመልአኩ ቀድሞውኑ ዐሳውቋቸው እንጂ መላእክት የቀደመ ዕውቀት በራሳቸው የላቸውም" ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም እሳቤ በዚህ ሒሳብ መረዳት ይቻላል። ተግባባን አይደል? አዎ! ግን ለመላእክትን ቀድሞ መናገሩ ለምን አስፈለገ? ይህ የአላህ ምርጫ ነው። እሩቅ ሳንሄድ እግዚአብሔር ምሥጢሩን ለባሪያዎቹ ለነቢያት ካልነገረ በቀር ምንም አያደርግም፦
አሞጽ 3፥7 *"በእውነት ጌታ እግዚአብሔር ምሥጢሩን ለባሪያዎቹ ለነቢያት ካልነገረ በቀር ምንም አያደርግም"*።

እግዚአብሔር ምንም ነገር ከማድረጉ በፊት ለነቢያቱ መናገሩ ችግር ከሌለው አላህ ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ሰውን እንደሚፈጥር ለመላእክት መናገሩ ችግር የለውም። ምነው እግዚአብሔር ሰውን ከመፈጠሩ በፊት ለመላእክት "እንፍጠር" ብሏቸው የለ እንዴ? የባሰ ጉድ፦
ኩፋሌ 4፥4 *ፈጣሪያችን* እግዚአብሔር ለእኛ *እንዲህ አለን*፦ “ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *”እንፍጠርለት”*።

“ፈጣሪያችን” የሚል ሃይለ-ቃል ይሰመርበት። "ፈጣሪያችን" ለእኛ "እንፍጠርለት" አለን እያለ ለሙሴ የሚተርክለት አንድ መልአክ ነው፦
ኩፋሌ 2፥4 *የፊቱ መልአክ በእግዚአብሔር ቃል ታዞ ሙሴን እንዲህ አለው*፦

በማለት እግዚአብሔር ለመላእክት እንፍጠርለት እንዳለ ይህ የኩፋሌ መጽሐፍ ይናገራል። የምጣዱ እያለ የዕንቅቡ ተንጣጣ። ቅቤ አንጣሪዋ እያለች ጎመን ቀንጣሿን ምች መታት።

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen
ወሠላሙ ዐለይኩም


>>Click here to continue<<

Tiriyachen | ጥሪያችን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)