* አስቸኳይ የእገዛ ጥሪ !
ለሐያት መዳን ምክንያት እንሁን 🙏
ሀያት ኢብራሂም ኡመር ትባላለች:: የ 11ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን እድሜዋ 17 ነው። በደረሰባት ከፍተኛ የሆነ የኩላሊት ህመም ዲያሌሲስ እየተደረገላት በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ትገኛለች።
በበሽታው መጠቃቷ ከታወቀበት እለት ጀምሮ ከበሽታው ጋር በትግል ላይ የምትገኝ ሲሆን ይህም ከቀን ወደ ቀን ሰውነቷን እያደከመው ይገኛል።
ታዳጊዋ የቀድሞ ጤንነቷ እንዲመለስ ያለው ብቸኛ አማራጭ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማድረግ ብቻ እንደሆነ ከህክምና ባለሙያዎች ተነግሯታል።
ለዚህ ህክምና ሁሉንም ሂደት (process) ጨምሮ እስከ 2,000,000 (ሁለት ሚሊየን) ብር ያስፈልጋታል!!!
ይህን ገንዘብ ለመሸፈን የሀያት ቤተሰቦች ወገኖቻችን እርዱን አግዙን እያሉ ወደ ህብረተሰቡ ጥሪ ያቀርባሉ።
ሐያት ወደ ሞት ስትሄድ እያያችሁ ዝም አትበሉኝ ለመዳኔ ምክንያት ሁኑ ትለናለች!
ከተረባረብን 2000 (ሁለት ሺህ) ሰው ሆነን 1000 (አንድ ሺህ) ብር ብልነግስ ልጃችን፣ እህታችን ድና ህልሟን ታሳካ ዘንድ ምክንያት እንሁናታለን። ሀያት ድና ትምህርቷን መቀጠል ትፈልጋለች። ደግሞ ለመዳኗ ሰብብ እንሆናለን።
የቻልነውን በሙሉ እህታችንን በገንዘብ እንርዳት፣ በገንዘብ ያልቻልን በፀሎት አብረናት እንሁን ፣ ሌላው ቢቀር መረጃውን ሼር በማድረግ ሊረዷት ወደሚችሉ ሰዎች አንድ እርምጃ እናቅርባት።
በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ
የአካውንት ስም:— ሀያት ኢብራሂም ዑመር
የኢትዮጲያን ግድ ባንክ:— 1000353443147
አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ:— 01425853981500
ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ :— 1000089014135
የሀያትን ቤተሰቦች በስልክ ለማግኘት
0983676776
0920942369
0912823605
@tikvahethmagazine
>>Click here to continue<<