TG Telegram Group Link
Channel: TIKVAH-ETHIOPIA
Back to Bottom
#Attention ⚠️

" ራኒቲዲን #ካንሰርን ሊያመጣ የሚችል ንጥረ ነገር በውስጡ በመገኘቱ ምክንያት #ታግዷል " - የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን

ለጨጓራ ተያያዥ ህመሞች በመድኃኒትነት ጥቅም ላይ ሲውል የነበረው ' ራኒቲዲን ' የተባለው መድሃኒት በኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል #ማገዱን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትልና የሕክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈጻሚ አስናቀች ዓለሙ ፤ " በመጀመሪያ ደረጃ በሌሎች ሀገር የወጡ ሪፖርቶችን አይተን ነበር። ስለዚህ በሀገራችንስ ይሄ መድሃኒት እንዴት ነው ? የሚለውን በማገናዘብ የላብራቶሪ ምርመራ አድርገናል " ብለዋል።

በዚህም መድሃኒቱ ካንሰር ሊያመጣ የሚችል ' N-nitrosodimethylamine ወይም NDMA ' የተሰኘ ንጥረ ነገር እንደተገኘበት መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ገልፀዋል።

" በመሆኑም ይህንን መድሃኒት ከምዝገባ ፋይላችን አውጥተናል። የተሰራጩ መድሃኒቶችም #እንዲሰበሰቡ እና ጥቅም ላይ እንዳይውሉ መልእክት አስተላልፈናል " ብለዋል።

" በዚህ በሰረትም ጥቅም እንዳይውል #ታግዷል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

" የጤና ባለሙያዎችም፣ የጤና ተቋማትም ሌሎች አማራጭ መድሃኒቶችን እንዲያዙ እና እንዲጠቀሙ ይህንን መድሃኒት #እንዳይጠቀሙ " ሲሉም አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia

🏆 የአውሮፓ ቻምፒዮን ማን ይሆን

⚽️ ሪያል ማድሪድ አይኑን ሌላ ዋንጫ ላይ ጥልዋል! ዶርትመንድ ከሞት ምድብ ድኖ ፒኤስጂን በመጣል ቅዳሜ ግንቦት 24 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በለንደን ዌንብሊ ለፍፃሜው ይገናኛሉ!

🔥 ዋንጫው የማን ነው?

👉 ይህንን ደማቅ ፍልሚያ በSS Football 222 በሜዳ ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DARMA

ግሬስ ኮንስትራክሽን ኬሚካልስ " DARMA " በሚባል ብራንድ የሚታወቁ ከ 15 በላይ የውሀ ስርገት መከላከያ፤ የወለል እና ግድግዳ ፊኒሺንግ አንዲሁም ከ ኮንክሪት ጋር የተያያዙ ማንኛውንም አይነት ኬሚካሎችን ከ8 አመታት በላይ በጥራት፤በፍጥነት እና በታማኝነት በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ 

ተጠቃሚዎች ላላቸው ጥቄዎች በነጻ የሚያማክር በመሀንዲሶች የታገዘ ቴክኒክ ክፍል መኖሩም ለብዙዎች መተማመንን ፈጠሮላቸዋል፡፡

ግሬስ ኮንስትራክሽን ኬሚካልስ ከግንቦት 22 እስከ 24 በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው የBIG 5 CONSTRUCT ETHIOPIA አለምአቀፍ ኤግዚቢሽን የወርቅ ደረጃ ስፖንሰር መሆኑንና ምርቶቹንም እንዲጎበኙ ሲጋበዝዎ በታለቅ ደስታ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በ ስ.ቁ 0964234444 ወይም 0929337886 ይደውሉ ወይም ወሎ ሰፈር አይቤክስ ሆቴል ጀርባ በሚገኘው ዋና ቢሮ ብቅ ይበሉ፡፡
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 " አሁን ላይ ያሉ ችግሮች ምፍትሄ እስካላገኙ  ስለ ምርጫ ማሰብ #ቀልድ ነው " - አቶ ግርማ በቀለ የሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሕብር) ሊቀ መንበር አቶ ግርማ በቀለ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታ አድረገዋል። Q. የዜጎች በሕይወት የመኖር መብት ጥሰትን በተመለከተ ስለሚነሱ ጉዳዮች የፓርቲዎ ግምገማ ምን ይላል ?   አቶ ግርማ…
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል።

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

Q. ከዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት አንፃር የፓርቲዎን ግምገማና መፍትሄውን ቢገልጹ ?

አቶ ጀሚል ሳኒ፦

“ ሰዎች በተደጋጋሚ ሕይወታቸውን እያጡ ነው። በዋና ከተማዋ ሲይቀር ሰዎች እየታሰሩ፣ እየታገቱ ነው።

የትኛውም ዜጋ የደህንነት ስሜት እየተሰማው አይደለም። 

መንግስት #በዋነኛነት የተመሠረተበትና እንዲሰራው ኃላፊነት የተሰጠው ስራ ከየትኛውም ቅድሚያ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ የተዘነጋ የሚመስልበት ዘመን ላይ ነን።

በመወያየትና በመነጋገር ጦርነትን ማስቆም ይገባል።

ሰላምን ከማስፈን ይልቅ #ስልጣንን_የመጠበቅ ፣ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት ነው አብዛኛው አቅም እየባከነ ያለው።

ከዚያ ይልቅ አገሪቱን በሚያሻግሩ ሀሳቦች ላይ አተኩሮ መስራት ያስፈልጋል።

ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦተ እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው። ”

Q. በሙስና ተዘፍቀው ስለሚገኙ ባለስልጣናት እንዲሁም በአጠቃላይ ስለብልሹ አሰራር ፓርቲዎ ምን ይላል ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ አሁን ላይ #ሀዘኔታዎች_የጠፉበት ፣ ሌላው ይቅርና የዜጎች ቤቶች ‘ሕገ ወጥ ናቸው’ ተብለው ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ላይ ገንዘብ የሚጠየቅበት ሁኔታ ነው ያለው። 

ከኢትዮጵያ Norm ሁላ ያፈነገጠበት ወቅት ላይ ነው ያለነው። በአብዛኛዎቹ መስሪያ ቤቶች የተለመደውን አይነት አሰራር ከመስራት ይልቅ ከእግሮች እጆች እየቀደሙ ነው።

#ሙስና_በግልጽ_እየተጠየቀ ፣ ቢሮ ውስጥ ሥራ አስፈጻሚዎች #በግልጽ_ድርድር እያደረጉበት ያለበት ሂደት ነው አሁን ያለው።

አለ የተባለ የትኛውም ችግርን ለመቅረፍ ላይከብድ ይችላል ፤ ነገር ግን ከተንሰራፋ የትኛውንም ችግር ልቅረፍ ማለት የማይታሰብ ይሆናል። 

ሙስና የሀገር ተቋርቋሪነትን፣ ስሜትን ያጠፋል።

እያየነው ያለውም ይሄው ነውና ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።”

Q. እንደ ፓርቲ የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የምስረታ ጉባዔ ባደረግንበት፣ የጉባዔውን ውጤትና የምርጫ ቦርድ ኮሮጆ ጭምር ይዘን በነበረበት ሰዓት ነው እስር የተጀመረው። ክፍለ አገርም አዲስ አበባም እስሮች አሉ። 

በአባል ደረጃ አንድ የፓርቲው አባል ከ5 ወራት በላይ ያለ ክስና ዋስትና በእስር ላይ ይገኛሉ። ከአባላቶች እስራትና ተንቀሳቅሶ ከመስራት ጋር ዘተያያዘ ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው።

ፓርቲውን የሚደግፉ አባላት #ወጣቶች_እየተላኩ ማስፈራሪያ ያደርሱባቸዋል።

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ሕገ መንግስቱን ያልከተለ በመሆኑ ምስረታው እንዲታገድ፣ ኢ - ሕገ መንግስታዊ ስራዎች በሰሩ ባለስልጣናት ላይ የመሰረትነው ክስ በቀጠሮ እየተጉላላ ነው ያለው። ”

Q. ሕዝቡ በኑሮ ውድነቱ ተማሯል። ለዚህም “ መንግስት ትኩረት አልሰጠም  ” የሚሉ ወቀሳዎች ይቀርባሉ። የፓርቲዎ ግምገማ ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የኑሮ ውድነት በራሱ የሚፈጠር ነገር አይደለም። እስካሁን ከላይ የተነጋገርንባቸው ነገሮች ናቸው እየገፉ የሚያመጡት። 

አንዲት አገር #በጦርነት ላይ ሆና ሚሊዮን ዶላሮችም ለጦርነት እያወጣች ፣ አርሶአደር ማምረትና በሰላም ወጥቶ መግባት ባልቻለበት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ የአቅም ፣ የብቃት ጉዳዮች የመጨረሻ ውጤታቸው የኑሮ ውድነቱ ማምጣት ነው።

እነዚህን ችግሮች ማጥፋት፣ መቀነስ ካልተቻለ የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ማስፈን አይቻልም። ”

Q. ስለምርጫ ያላችሁ አስተያዬት ምንድን ነው ? በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?


“ ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው፣ አጀንዳውም የሚያዘው ከሚደረገው #የፓርላማ እና #የክልል_ምክር_ቤቶች ጋር በተገናኘ ነው። 

ይሄ ስርዓቱን ለመቀየር የሚያስችል ብቸኛው መንገድ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ምርጫ በየአካባቢው ማድረግ ያስፈልጋል። የአካባቢ ምርጫ የተደረገው ከ8 ዓመታት በፊት ነው።

የአካባቢ ምርጫ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።

አሁን ባለንበት ሁኔታ ላይ #ምርጫ ሊደረግ ይችላል ብሎ ማለት ትንሽ አዳጋች ነው። ”

◾️በቀጣዩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፓርቲ የሰጠው ቃል ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በመጪው ሰኔ ወር የሚሰጠው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ን በድጋሜ ለሚወስዱ ተፈታኞች መልዕክት አስተላልፏል።

1ኛ. በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የነበረና አሁን በድጋሜ ለመፈተን ማመልከት ለሚፈልጉ፤

2ኛ. ከሰኔ 2015 ዓ.ም በፊት #የሕግ_መውጫ_ፈተና ወስደው የማለፍያ ነጥብ ያለገኙ አሁን በድጋሚ ለመውሰድ ለሚፈልጉ ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርስቲያቸው ለትምህርት ሚኒስቴር የተላከላቸው አመልካቾች፤

ምዝገባው እስከ ግንቦት 25/ 2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ገልጿል።

ተፈታኞች በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ብቻ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ ተብሏል።

ሚኒስቴሩ ፦

➡️ ከላይ ከተገለጸው ጊዜ ውጭ የሚቀርቡ የምዝገባ ጥያቄዎች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው አሳስቧል።

➡️ በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያልመጡ አሁን በድጋሜ መፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች የሚጠበቅባቸውን የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር ብቻ መፈጸም አለባቸው ተብሏል።

➡️ ከሰኔ 2015 ዓ/ም በፊት ለሕግ መውጫ ፈተና ተቀምጠው በድጋሜ ለመፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርሲቲያቸው መላኩን በማረጋጥ የሚጠበቅባቸውን #የአገልግሎት_ክፍያ ለዚሁ ጉዳይ ብቻ በተከፈተው የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር ➡️1000553176097 ገቢ በማድረግ ደረሰኙን በግልፅ በሚታይ #ስካን_ኮፒ በማድረግ በ [email protected] ኢሜል አድራሻ እንዲልኩ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Big 5 Construct Ethiopia's opening ceremony today was honored by the presence of H.E. Temesgen Tiruneh, Deputy Prime Minister of Ethiopia and H.E. Chaltu Sani, Minister, Ministry of Urban and Infrastructure who shared their insights on the construction industry and officially declared the show open.

Register now for free entry and join the exhibition happening at the Millennium Hall until 1 June 2024.

Click here: https://bit.ly/3UsrL5I
ኢትዮ ቴሌኮም ተጨማሪ #በ77_ከተሞች የ4G LTE አገልግሎት ጀመረ.።

ኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ የዳታ አጠቃቀም ይታይባቸዋል ባላቸው 77 ከተሞች አዲስ የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት አስጀምሯል።

በኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢትዮ ቴሌኮም ኔትዎርክ የ4ጂ LTE አገልግሎት ተጠቃሚ ከተሞች ብዛት 417 መድረሱንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጠቅሷል።

(የከተሞቹን ዝርዝር ከላይ በምስሉ ላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ማንኛውንም ሰው #ከሀገር_እንዳይወጣ የማገድ ስልጣንን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤትን በዋና ዳይሬክተርነት ለሚመራ ኃላፊ የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለህ/ ተ/ ም/ ቤት  ቀርቧል።

የአዋጅ ማሻሻያው ምን ይዟል ?

ማሻሻያው ማንኛውንም ሰው ከሀገር እንዳይወጣ የማገድ ስልጣን ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ይሰጣል።

ነባሩ ህግ ምን ይላል ?

" ማንኛውም ሰው #ከኢትዮጵያ_እንዳይወጣ ሊታገድ የሚችለው በህግ መሰረት #በፍርድቤት ሲታዘዝ ብቻ ነው " ይላል።

ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው የአዋጅ ማሻሻያ በነባሩ ህግ ላይ የተቀመጠውን የፍርድ ቤትን " #ብቸኛ_ስልጣን " የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤትን በዋና ዳይሬክተርነት ለሚመራ ኃላፊ በተጨማሪነት #ያጋራ ነው።

ማሻሻያው የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ፦

⚫️ ከሚመለከታቸው የደህንነት አገልግሎት እና ህግ አስከባሪ አካላት ከሚያገኘው መረጃ ወይም አገልግሎቱ በራሱ ከሚያገኘው መረጃ በመነሳት ፤

⚫️ በብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ ሊቀለበስ የማይችል ግልጽና ድርስ የሆነ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል ሁኔታ መኖሩን ሲያምን፤ ማንኛውም ሰው ከሀገር እንዳይወጣ ማገድ ይችላል ሲል ደንግጓል። 

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ፤ " ከሀገር እንዳይወጣ ያገደውን ሰው ይዞ የሚያቆይ ከሆነ ፍ/ቤት መቅረቡን ማረጋገጥ አለበት "ም ይላል የአዋጅ ማሻሻያው። 

ዜጎች ከሀገር እንዳይወጡ የማገድ ስልጣን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፤ በነባሩ ድንጋጌ ምክንያት እየደረሰ ያለውን " ከፍተኛ ጉዳት " ለመቅረፍ እንደሆነ በማሻሻያው ላይ ሰፍሯል።

አሁን በስራ ላይ ባለው አዋጅ መሰረት " ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ እስኪገኝ ድረስ በብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ ወይም ሊያደርሱ የሚችሉ ሰዎች ከሀገር እየወጡ ከተጠያቂነት እያመለጡ በሀገራችን ብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ነው " ሲል የረቂቅ አዋጁ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፦

ማሻሻያ አዋጁ " #አስተዳደራዊ_ቅጣት " አንቀጽ ይዟል።

" ከጊዜ ወደ ጊዜ በህገ ወጥ መንገድ በሀገራችን ውስጥ የሚኖሩ የውጭ ሀገር ዜጎች እየተበራከቱ፤ በህገ ወጥ ድርጊቶች እየተሳተፉ ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩ በመሆኑ በአስተዳደራዊ ቅጣት በመቅጣት ከህገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ሲል ያስረዳል።

በዚህም በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ሀገር ዜጎችን " በጥቁር መዝገብ እንዲመዘገቡ እና ከሀገር እንዲወጡ ማድረግ ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲመጡ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ የሆነ ሚና " እንዳለው ተብራርቷል።

#የሚኒስትሮች_ምክር_ቤት በሚያወጣው ደንብ አማካኝነት፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መ/ቤት አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጥል በአዋጅ ማሻሻያው ስልጣን ተሰጥቶታል።

" ይህን አዋጅ አሊያ በዚህ አዋጅ መሰረት የወጣ ደንብ ወይም መመሪያን የጣሰ ማንኛውም ሰው ፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድበታል " ይላል ማሻሻያው።

Credit:
#EthiopiaInisider 
#JournalistTesfalemWoldeyes

@tikvahethiopia
#ሬዚደንት #JU

“ የ3 ወራት ያህል ደመወዝ አልተከፈለንም ” - የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሬዚደንት ሀኪሞች

“ ይህ ጉዳይ ጤና ሚኒስቴርን ነው የሚመለከተው ” - ዩኒቨርሲቲው

በ2016 ዓ/ም በጤና ሚኒስቴር #በጅማ_ዩኒቨርሲቲ  ተመድበው በሆስፒታሉ ሥራና ስፔሳላይዜሽን ስልጠና የሚወስዱ 70 የአንደኛ ዓመት ሬዚደንት ሀኪሞች የ3 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ቅሬታ አቅርበዋል። 

“ የ3 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም። ከፍተኛ ችግርና ስቃይ ውስጥ ወድቀናል ” ያሉት ቅሬታ አቅርቤዎቹ፣ ጉዳዩ የሚመለከተውን አካል ቢያነጋግሩም ‘ መፍትሄ እየፈለግን ነው ፤ ዩኒቨርሲቲው በጀት የለውም ’ እንደተባሉ ገልጸዋል።

መጀመሪያ 100 ሬዚደንት ሀኪሞች እንደነበሩ ፤ በኋላ ግን ለቀው ለመሄድ በመገደዳቸው አሁን ላይ የቀሩት 70 ብቻ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ቤተሰብ ጭምር ይዘው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሄዱ ሬዚደንት ሀኪሞችም እንዳሉ ፤ የሚተዳደሩት ከደመወዝ በሚያገኙት ገቢ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ በጣም ከፍተኛ ችግር ውስጥ ነው ያለነው። ደመወዙ በዚህ ሳምንት ሊገባልን ይገባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ፣ “ ጤና ሚኒስቴርን ነው የሚመለከተው። እኛን አይመለከትም ” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

በጉዳዩ ላይ ምላሽ ለመጠየቅ ወደ #ጤና_ሚኒስቴር የተደረገው ሙከራ ኃላፊዎቹ ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ለጊዜው ቃላቸውን ማካተት አልተቻለም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

የነጻ (Free) ወይም የህዝብ (Public)ዋይፋይ ስጋቶች እና መወሰድ ያለባቸው ጥንቃቄዎች።

የተለያዪ ጠቃሚ ምክሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ።

https://hottg.com/BoAEth
የአየር ሰዓት ለመሙላት ፈልገው የማይችሉበት ሁኔታ ቢፈጠር፤ *810# ላይ በመደወል የአየር ሰዓት እና የጥቅል ብድር አገልግሎታችንን ተጠቅመው ግንኙነትዎን መቀጠል ይችላሉ፡፡

ቀጣይ ከሚሞሉት የአየር ሰዓት ላይ 10% የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላሉ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#Ethiopia

በዛሬው ዕለት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ አካሂዶ ውሳኔዎች አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ አንዱ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ አዋጅን የሚመለከት ነው።

ም/ቤቱ " ከህጋዊና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ የቆዩ የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ እነዚህን አካላት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ አድርጎ ለመመዝገብ የሚያስችል ስርዓት በነባሩ አዋጅ ላይ አልተካተተም " ብሏል።

" በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ፍላጎት በሚያሳዩበት ጊዜ መልሶ መመዝገብ የሚያስችል ስርዓት ለመዘርጋት ረቂቅ የአዋጅ ማሸሻያ ተዘጋጅቶ ቀርቧል " ሲል ገልጿል።

ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

ሌላው ደግሞ ምክር ቤቱ በህገ ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አድርጎ ስለማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በቀረበው አዋጅ ላይ መወያየቱን አሳውቋል።

" በወንጀል የተገኘን ንብረት ህጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀል የደህንነት ስጋት ከመሆኑ በተጨማሪ የፋይናንስ ስርዓቱ የተረጋጋ፣ ግልጸኝነት ያለው፣ ጤናማና ቀልጣፋ እንዳይሆን የሚያደርግ ነው " ብሎታል።

ይህን ወንጀል ለመከላከልና ለመቆጣጠር ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱን የገለጸው ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጁ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን አመልክቷል።

(ተጨማሪ የምክር ቤቱን የስብሰባ ውሳኔዎች ከላይ ያንብቡ)

@tikvahethiopia
HTML Embed Code:
2024/05/31 08:49:17
Back to Top