TG Telegram Group & Channel
TIKVAH-ETHIOPIA | United States America (US)
Create: Update:

#ጋና #ፀረግብረሰዶም

ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል።

ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው።

ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው።

በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል።

በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦
- በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ
- የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር
- ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ
- ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል።

ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል።

የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው።

ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ልታጣ ትችላለች ተብሏል።

@tikvahethiopia

#ጋና #ፀረግብረሰዶም

ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል።

ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው።

ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው።

በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል።

በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦
- በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ
- የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር
- ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ
- ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል።

ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል።

የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው።

ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ልታጣ ትችላለች ተብሏል።

@tikvahethiopia


>>Click here to continue<<

TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)