TG Telegram Group & Channel
TIKVAH-ETHIOPIA | United States America (US)
Create: Update:

#Update #ራያ

° “ ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር

° “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል ” - የተጎጂ ቤተሰብ

በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ተቀሰቀሰ የተባለውን ተኩስ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ሆነው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢ ከፍተኛ አመራር ከትላንት ወዲህ ያለውን ሁኔታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።

እኚሁ አመራር ፤ “ ዛሬ አፍሪካ ህብረት መጥተው ማን ስምምነቱ እንደጣሰ ተመልክተዋል። አፍሪካ ህብረት እያንዳንዱን ችግር አይተውታል ” ብለዋል።

“ ዛሬ ተኩስ የለም። የያዙት ቦታ አሁንም አለቀቁም። ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል። መከላከያ ያለውን እውነታ አስረድቷቸዋል ” ሲሉ አክለዋል።

“ የሞተውን ዛሬ በክብር ቀብረነዋል። ማቹ ተፈራ ፍቃዱ ይባላል። የሁልግዜ ለምለም ቀበሌ ነዋሪ ነው። ቀብሩም ከቀኑ 7፡00 በጎልአጆ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል። ሪፈር የተላኩ አልተመለሱም ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተኩሱ ጉዳት ደርሶባቸው ሪፈር ተጽፎላቸዋል ከተባሉት ሁለት ቁስለኞች መካከል የአንዱ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል። በአላማጣ አዋሳኝ በኩል ድንበር ላይ ቆሞ እያለ ነው በእነርሱ (በህወሓት) በኩል ጥቃት የደሰበት” ብለዋል።

“ በጣም ከፍተኛ ጉዳት አለው ሁለቱም እጆቹ ከኋላውም ቀላል ጉዳት ደርሷል። ግን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሁለቱ እጆቹ ላይ ነው። ወደ ደሴ ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎለት እንደገና ደሙ አልቆም ሲል ወልዲያ ሆስፒታል ከትላንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ (መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ/ም) 7፡00 ገብቶ ነበር። ከዚያ በኋላም ወደ ግል ክሊኒክ ገብቷል። ሁለቱም እጆቹ ላይ ስለሆነ በጣም ስቃይ አለው ” ሲሉ አክለዋል።

" በድንበራችን ላይ መጥተው ነው ጥቃህት ያደረሱት" ብለው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

የትግራይ እና የአማራ ክልል አዋሣኝ ቦታ የሚገኙ የስራ ኃላፊዎች በራያ በተፈጠረው ጉዳይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ።

በትግራይ ክልል በኩል ያሉ አመራሮች ሰሞነኛውን ተኩስ የከፈቱት የአማራ ክልል ታጣቂዎች እንደሆኑ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ግጭቱም ሆን ተብሎ  ፦
- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ
- የትግራይ ማህበረሰብ ተወካዮች ከጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ያደረጉት ውይይትና የአማራ እና የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንቶች በፕሪቶሪያ ውል አተገባበር ዙሪያ የፈጠሩት መድረክን ተከትሎ 'ውሉ ተግባራዊ ይሆናል' የሚል ስጋት ስለፈጠረባቸው ነው " ብለዋል።

" አሁንም የአማራ ክልል ታጣቂዎች ለቀጣይ ትንኮሳ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ደርሰንበታል " ብለዋል።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ውል እንዲከበርና የአማራ ክልል ታጣቂዎች በኃይል ከያዟቸው የትግራይ አካባቢዎች እንዲወጡ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

እስካሁን ድረስ በሁለቱም በኩል በክልል ደረጃ ስለ ጉዳዩ ያወጡት መግለጫ የለም። የፌዴራል መንግሥትም ያለው ነገር የለም።

መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው።

@tikvahethiopia

TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ራይ " ግጭቱ ከ20 ደቂቃ በላይ አልፈጀም፤ በግጭቱ የሞተ ሰውም የለም  " - በትግራይ ደቡባዊ ዞን የራያ ጨርጨር አስተዳዳሪ አቶ ግደይ ካልኣዩ " የአማራ ታጣቂዎች በትግራይ ግዛት ውስጥ የፈፀሙት ትንኮሳ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት  እንዲያስቆመው ተደርጓል " - የትግራይ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሓለፎም የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባናል ጥያቄ በሚያነሱበት…
#Update #ራያ

° “ ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር

° “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል ” - የተጎጂ ቤተሰብ

በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ተቀሰቀሰ የተባለውን ተኩስ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ሆነው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢ ከፍተኛ አመራር ከትላንት ወዲህ ያለውን ሁኔታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።

እኚሁ አመራር ፤ “ ዛሬ አፍሪካ ህብረት መጥተው ማን ስምምነቱ እንደጣሰ ተመልክተዋል። አፍሪካ ህብረት እያንዳንዱን ችግር አይተውታል ” ብለዋል።

“ ዛሬ ተኩስ የለም። የያዙት ቦታ አሁንም አለቀቁም። ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል። መከላከያ ያለውን እውነታ አስረድቷቸዋል ” ሲሉ አክለዋል።

“ የሞተውን ዛሬ በክብር ቀብረነዋል። ማቹ ተፈራ ፍቃዱ ይባላል። የሁልግዜ ለምለም ቀበሌ ነዋሪ ነው። ቀብሩም ከቀኑ 7፡00 በጎልአጆ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል። ሪፈር የተላኩ አልተመለሱም ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተኩሱ ጉዳት ደርሶባቸው ሪፈር ተጽፎላቸዋል ከተባሉት ሁለት ቁስለኞች መካከል የአንዱ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል። በአላማጣ አዋሳኝ በኩል ድንበር ላይ ቆሞ እያለ ነው በእነርሱ (በህወሓት) በኩል ጥቃት የደሰበት” ብለዋል።

“ በጣም ከፍተኛ ጉዳት አለው ሁለቱም እጆቹ ከኋላውም ቀላል ጉዳት ደርሷል። ግን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሁለቱ እጆቹ ላይ ነው። ወደ ደሴ ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎለት እንደገና ደሙ አልቆም ሲል ወልዲያ ሆስፒታል ከትላንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ (መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ/ም) 7፡00 ገብቶ ነበር። ከዚያ በኋላም ወደ ግል ክሊኒክ ገብቷል። ሁለቱም እጆቹ ላይ ስለሆነ በጣም ስቃይ አለው ” ሲሉ አክለዋል።

" በድንበራችን ላይ መጥተው ነው ጥቃህት ያደረሱት" ብለው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

የትግራይ እና የአማራ ክልል አዋሣኝ ቦታ የሚገኙ የስራ ኃላፊዎች በራያ በተፈጠረው ጉዳይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ።

በትግራይ ክልል በኩል ያሉ አመራሮች ሰሞነኛውን ተኩስ የከፈቱት የአማራ ክልል ታጣቂዎች እንደሆኑ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ግጭቱም ሆን ተብሎ  ፦
- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ
- የትግራይ ማህበረሰብ ተወካዮች ከጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ያደረጉት ውይይትና የአማራ እና የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንቶች በፕሪቶሪያ ውል አተገባበር ዙሪያ የፈጠሩት መድረክን ተከትሎ 'ውሉ ተግባራዊ ይሆናል' የሚል ስጋት ስለፈጠረባቸው ነው " ብለዋል።

" አሁንም የአማራ ክልል ታጣቂዎች ለቀጣይ ትንኮሳ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ደርሰንበታል " ብለዋል።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ውል እንዲከበርና የአማራ ክልል ታጣቂዎች በኃይል ከያዟቸው የትግራይ አካባቢዎች እንዲወጡ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

እስካሁን ድረስ በሁለቱም በኩል በክልል ደረጃ ስለ ጉዳዩ ያወጡት መግለጫ የለም። የፌዴራል መንግሥትም ያለው ነገር የለም።

መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው።

@tikvahethiopia


>>Click here to continue<<

TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)