TG Telegram Group & Channel
TIKVAH-ETHIOPIA | United States America (US)
Create: Update:

#ይነበብ

ኢትዮጵያ ውስጥ የካንሠር በሽታ #የከፋ_ደረጃ ላይ እየደረሰ በመሆኑ ማኅበረሰቡ ልዩ ትኩረት እንዲያደርግ ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሠር ሶሳይቲ አሳስቧል።

የካንሠር ሕሙማን ቁጥር እየጨመረ ያለው ለምንድነው ?

የድርጅቱ ሜዲካል ዳይሬክተር ናትናኤል አለማየሁ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የዓመቱ ወደ ከ60,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በካንሠር በሽታ ይያዛሉ። ከእነዚህ ውስጥ 44,000 በላይ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን ሕይወታቸውን ያጣሉ።

በበሽታው የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ያለበት ምክንያት ፦

- ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ መስፋፋት፣

- በቂ ያልሆነ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ እና የአኗኗር ዘይቤ መቀየር

- የሲጋራ ፣ ሽሻ አጫሾች መበራከት ፣ የአልኮል መጠቀም

- ለተለያዩ ኬሚካሎች መጋለጥ፣

- ከተለያዩ #ኢንᎊክሽኖች ጋር የሚያያዙ የካንሰር አይነቶች መበራከት

- በወቅቱ ሕክምና ሳያገኙ የኖሩ ሰዎች አሁን አሁን ወደ ሕክምና እየመጡ በመሆኑና ሌሎች መሰል ምክንያቶች ናቸው።

ወደ ሕክምና የሚመጡት 70 በመቶ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን የህመሙ ደረጃ ከፍ ካለ እና ስር ከሰደደ በኃላ ነው።

ዶ/ር ናትናኤል ፤ " ከካንሠር ሕመም መዳን ይቻላል " ያሉ ሲሆን ይህም ተገቢዉን ምርመራ እና ህክምና በተገቢዉ ጊዜ ማድረግ ሲቻል ፣ ስር ሳይሰድ ህክምና ካገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ለህሙማን ሁለንተናዊ የሆነ እንክብካቤ እና ድጋፍ ሁሉም ካለዉ ቀንሶ እንዲያደርግ ፣ ማህበረሰቡ በካንሰር ላለመያዝ አጋላጮቹን መከላከል እና ቅድመ ምርመራ ላይ እንዲያተኩር አሳስበዋል።

@tikvahethiopia

TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ይነበብ

ኢትዮጵያ ውስጥ የካንሠር በሽታ #የከፋ_ደረጃ ላይ እየደረሰ በመሆኑ ማኅበረሰቡ ልዩ ትኩረት እንዲያደርግ ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሠር ሶሳይቲ አሳስቧል።

የካንሠር ሕሙማን ቁጥር እየጨመረ ያለው ለምንድነው ?

የድርጅቱ ሜዲካል ዳይሬክተር ናትናኤል አለማየሁ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የዓመቱ ወደ ከ60,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በካንሠር በሽታ ይያዛሉ። ከእነዚህ ውስጥ 44,000 በላይ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን ሕይወታቸውን ያጣሉ።

በበሽታው የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ያለበት ምክንያት ፦

- ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ መስፋፋት፣

- በቂ ያልሆነ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ እና የአኗኗር ዘይቤ መቀየር

- የሲጋራ ፣ ሽሻ አጫሾች መበራከት ፣ የአልኮል መጠቀም

- ለተለያዩ ኬሚካሎች መጋለጥ፣

- ከተለያዩ #ኢንᎊክሽኖች ጋር የሚያያዙ የካንሰር አይነቶች መበራከት

- በወቅቱ ሕክምና ሳያገኙ የኖሩ ሰዎች አሁን አሁን ወደ ሕክምና እየመጡ በመሆኑና ሌሎች መሰል ምክንያቶች ናቸው።

ወደ ሕክምና የሚመጡት 70 በመቶ የሚሆኑት የካንሠር ሕሙማን የህመሙ ደረጃ ከፍ ካለ እና ስር ከሰደደ በኃላ ነው።

ዶ/ር ናትናኤል ፤ " ከካንሠር ሕመም መዳን ይቻላል " ያሉ ሲሆን ይህም ተገቢዉን ምርመራ እና ህክምና በተገቢዉ ጊዜ ማድረግ ሲቻል ፣ ስር ሳይሰድ ህክምና ካገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ለህሙማን ሁለንተናዊ የሆነ እንክብካቤ እና ድጋፍ ሁሉም ካለዉ ቀንሶ እንዲያደርግ ፣ ማህበረሰቡ በካንሰር ላለመያዝ አጋላጮቹን መከላከል እና ቅድመ ምርመራ ላይ እንዲያተኩር አሳስበዋል።

@tikvahethiopia


>>Click here to continue<<

TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)