This is Coca-Cola Arena
ይህ Coca Cola arena ነው። በዚህ መድረክ የዓለማችን እውቅና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ብቻ ናቸው መቆም የሚችሉት። ከምስራቅ አፍሪካ ግን እስካሁን ማንም በዚህ መድረክ ቆሞ ስራውን ማቅረብ አልቻለም። የምስራቅ አፍሪካ ሰዎችም ለዚህ እድል ቀድመው አልበቁም።
ኢትዮጵያውያን ግን እነሆ በአንድ ልንሰበሰብበት ነው።
ዓለም የተስማማባቸው እውቅ ሰዎች አስደንጋጭ ዝግጅቶችን ባቀረቡበት በዚህ መድረክ ላይ ለአፍሪካውያን ወጣቶች ተምሳሌት የሆነው፡ በማንኛውም መድረክ ላይ ብቻውን በመቆም እልፍ አድናቂዎችን መሰብሰብ የተቻለው፡ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉስ የሆነው፡ የክብር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ በዚህ በግዙፍ አዳራሽ ስራውን ያቀርባል። ከምስራቅ አፍሪካም ቀዳሚ በመሆን በዓለም የኪነጥበብ ታሪክ ሲዘከር ይኖራል።
በዚህ ታሪካዊ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ለመታደም ከዓለም ጫፍ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እየተጠራሩ ይገኛሉ። በዕለቱ ዓለም እየሰማ ኢትዮጵያ በታላቅ የብሔራዊ ስሜት ትጠራለች ባንዲራዋም በባዕድ ምድር ከፍ ብሎ ይውለበለባል። ምን ይሄ ብቻ…! የኢትዮጵያ ነገሥታቶች ስማቸው በታላቅ ኩራትና በጀግንነት ስሜት ይወሳል። ምክኒያቱም ያለንን ማንነት የሰጡን እነርሱ ናቸውና።
✍#ታታ_አፍሮ (ነፃ ብዕር)
>>Click here to continue<<