"ውብ ቃላቶችን አትመኑ። እውነቱን ከክስተቶች አንደበት ውሰዱ።" ነጂብ መህፉዝ
አንዳንዶቹ ሲያደንቁህ ከሰማይና ከጨረቃ ውበት ጋር ያመሳስሉሃል፣ ውዴታቸውን ሲገልፁልህ ደግሞ ላንተ መስዋዕት እስከመሆን ያዘልቁሃል። ያ ሁሉ የቃል ውዳሴና ውዴታ በፈታኝ ተግባር ውስጥ ግን ኦና ይሆናል። ሁሌም ከጎንህ እንደሆኑ ቢነግሩህም ሲፈልጉህ እንጂ በቁም ነገር ስትፈልጋቸው አታገኛቸውም። ክስተቶች እውነትን ይገልጣሉ። በቃላት የተከሸኑ ውዴታዎችም በአንድ ወቅት በተግባር ይፈተናሉ።
@qteloch
፨Join it፨
@qteloch
>>Click here to continue<<