TG Telegram Group & Channel
FŰŇ_ŽØÑĘ 😂😱 | United States America (US)
Create: Update:

⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.

⚀ ክፍል አስራ ሰባት⚀ 1⃣7⃣




እማ ምነው ትርሃሴ ቆየች!? " አልኳት ቻርጀሩ መቀበል አለመቀበሉን እያረጋገጥኩ።
"አሁን ትመጣልህ የለ!" ብላኝ ሳትጨርስ
"እማ እንዴት ነሽልኝ እናቴ !" እያለች ገባች። ከመቅበጥበጧ የተነሳ የምትዘፍን ነበር የምትመስለው።
"ሚሚዬ እንዴት ዋልሽ ልጄ?"
"አለውልሽ ኡፍፍፍ ደክሞኛል እማ ውሃ ስጪኝ በማሪያም?"
"እሺ እሺ ወንድምሽን ሰላም አትዪውም እንዴ? ምነው ትርሃሴ?" አለች
ባክሽ እኔ የማንንም ሽንኩርታም ሰላም ስል ጊዜዬን አላቃጥልም! You know time is the gold"አለች በጎሪጥ እየተመለከተችኝ።
"ማንን ነው አንቺ? አይጥ!"አልኳት ኮስተር ለማለት እየታገልኩ።
"እኔ ግሩም ብዬ ጠርቼሃለው ሽንኩርታም!" አለች ጀነን እንዳለች።
ሚሚዬ እግዚአብሔርን ይሄን ሽንኩርት አበላሻለሁ! ጥጋብሽን ቀንሺ "አልኳት።
"ወንድ ነኻ ዝም ስልህ የፈራሁህ መሰለህ? አመዳም! ግምባራም! ሂሽ ሽንኩርታም!!" አለች።
ከምከትፈው ሽንኩርት ላይ በእጄ ዘግኜ ወስጄ ላበላት ታስታገል ጮኸች።
"ግሩሜ በእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ግሩሜ የኔ ወንድም በእግዚአብሔር አዪዪዪ እማ ተው በይው እንጂ ኧረ በማሪያም እማ?!" አለች እየታገለችኝ
"አንቺ ማን ነገር ፈልጊው አለሽ እና ነው?" አለች እናቴ
"ኧረ እማ አበላኝ እኮ በእግዚአብሔር ቱ ምን አይነት ገገማ ነው በእግዚአብሔር " አለች ፊቷን ጭፍግግ አድርጋ ያበላዋትን ሽንኩርት እየተፋች
"አሁንም እንዳላበላሽ ዋ!"
"ሂድ ወደዛ ሽንኩርታም! ወንድ ነህ ግሩሜ አሁንማ"አለች ወደ እናቴ እየርጠች። እናቴን መሃል አድርገን ተያየን።
"ምነው ጌታዬ ብትተዉ ሽንኩርቱንም በትናችሁ ጨረሳችሁት እኮ አዬ ልጅነት"አለች ወደ እኔ ዞራ።
"አንቺም እረፊ ተሞጣሙጠሽ ስታበቂ እኔን አትጥሪኝ ደቃቃ" አለቻት በፍቅር ቁጣ
"እማ ግን ሁል ጊዜ እኔ ላይ ነው አይደል የምትጮሂው? እንዴ......" ትርሃስ እየተነጫነጨች ስልኬ ጮኸ።አነሳሁት።
"አቤት ፍሌሜ!" አልኩኝ
ከወዲያኛው የስልኩ ጫፍ
"ግሩሜ በፍጥነት ቤት ና እፈልግሃለው " የሚል የፍሌሜን ድምፅ እንደሰማው ስልኩ ተዘጋ።
ግራ ገባኝ ተነስቼ ከነፍኩ።
የትርሃስ ስድብና ንጭንጭ እስክወጣ እየተከተለኝ ነበር።


ክፍል አስራ ስምንት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @ABDSEWANTED

አንብባችሁ ሼር አድርጉት!!

"SHARE" @ONLYZEGET

⊶⊷⊶⊷❍ ፍሌም ❍⊶⊷⊶⊷

˙·٠•● ተከታታይ ልቦለድ●•٠·˙
.
ደራሲ ሲራክ
.

⚀ ክፍል አስራ ሰባት⚀ 1⃣7⃣




እማ ምነው ትርሃሴ ቆየች!? " አልኳት ቻርጀሩ መቀበል አለመቀበሉን እያረጋገጥኩ።
"አሁን ትመጣልህ የለ!" ብላኝ ሳትጨርስ
"እማ እንዴት ነሽልኝ እናቴ !" እያለች ገባች። ከመቅበጥበጧ የተነሳ የምትዘፍን ነበር የምትመስለው።
"ሚሚዬ እንዴት ዋልሽ ልጄ?"
"አለውልሽ ኡፍፍፍ ደክሞኛል እማ ውሃ ስጪኝ በማሪያም?"
"እሺ እሺ ወንድምሽን ሰላም አትዪውም እንዴ? ምነው ትርሃሴ?" አለች
ባክሽ እኔ የማንንም ሽንኩርታም ሰላም ስል ጊዜዬን አላቃጥልም! You know time is the gold"አለች በጎሪጥ እየተመለከተችኝ።
"ማንን ነው አንቺ? አይጥ!"አልኳት ኮስተር ለማለት እየታገልኩ።
"እኔ ግሩም ብዬ ጠርቼሃለው ሽንኩርታም!" አለች ጀነን እንዳለች።
ሚሚዬ እግዚአብሔርን ይሄን ሽንኩርት አበላሻለሁ! ጥጋብሽን ቀንሺ "አልኳት።
"ወንድ ነኻ ዝም ስልህ የፈራሁህ መሰለህ? አመዳም! ግምባራም! ሂሽ ሽንኩርታም!!" አለች።
ከምከትፈው ሽንኩርት ላይ በእጄ ዘግኜ ወስጄ ላበላት ታስታገል ጮኸች።
"ግሩሜ በእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ግሩሜ የኔ ወንድም በእግዚአብሔር አዪዪዪ እማ ተው በይው እንጂ ኧረ በማሪያም እማ?!" አለች እየታገለችኝ
"አንቺ ማን ነገር ፈልጊው አለሽ እና ነው?" አለች እናቴ
"ኧረ እማ አበላኝ እኮ በእግዚአብሔር ቱ ምን አይነት ገገማ ነው በእግዚአብሔር " አለች ፊቷን ጭፍግግ አድርጋ ያበላዋትን ሽንኩርት እየተፋች
"አሁንም እንዳላበላሽ ዋ!"
"ሂድ ወደዛ ሽንኩርታም! ወንድ ነህ ግሩሜ አሁንማ"አለች ወደ እናቴ እየርጠች። እናቴን መሃል አድርገን ተያየን።
"ምነው ጌታዬ ብትተዉ ሽንኩርቱንም በትናችሁ ጨረሳችሁት እኮ አዬ ልጅነት"አለች ወደ እኔ ዞራ።
"አንቺም እረፊ ተሞጣሙጠሽ ስታበቂ እኔን አትጥሪኝ ደቃቃ" አለቻት በፍቅር ቁጣ
"እማ ግን ሁል ጊዜ እኔ ላይ ነው አይደል የምትጮሂው? እንዴ......" ትርሃስ እየተነጫነጨች ስልኬ ጮኸ።አነሳሁት።
"አቤት ፍሌሜ!" አልኩኝ
ከወዲያኛው የስልኩ ጫፍ
"ግሩሜ በፍጥነት ቤት ና እፈልግሃለው " የሚል የፍሌሜን ድምፅ እንደሰማው ስልኩ ተዘጋ።
ግራ ገባኝ ተነስቼ ከነፍኩ።
የትርሃስ ስድብና ንጭንጭ እስክወጣ እየተከተለኝ ነበር።


ክፍል አስራ ስምንት ይቀጥላል........

ደራሲ C-ራክ
comment ፦ @ABDSEWANTED

አንብባችሁ ሼር አድርጉት!!

"SHARE" @ONLYZEGET


>>Click here to continue<<

FŰŇ_ŽØÑĘ 😂😱




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)