#ኢሰመጉ
የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት እንደገና እንዲፈተሽላቸው ጥያቄ ላቀረቡ ተማሪዎች መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ጠይቋል።
"የፈተናው ውጤት ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች ውጤታቸው እንደገና እንዲፈተሽላቸው ለሚመለከተው አካል ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ" ጉባኤው ገልጿል።
"በመሆኑም የሚመለከተው ክፍል የተማሪዎቹን ጥያቄ በመመርመር አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው" ጉባኤው አሳስቧል።
በፈተናው ውጤት ዙሪያ "ከተለያዩ አካላት የሚሰነዘሩ ሃሳቦች ማኅበረሰቡን ግራ እያጋቡ እና የተማሪዎቹንም ስነ ልቦና እየጎዱ በመሆናቸው የሚመለከተው አካል ተገቢውን ማብራሪያ እንዲሰጥ እና የእርምት እርምጃ እንዲወስድ" ኢሰመጉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጥሪውን አቅርቧል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት
@minesterofeducation
>>Click here to continue<<