#Update
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ጊዜ እንዲዘገይ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።
የአብን ማዕከላዊ ኮሚቴ መጋቢት 09 እና 10/2014 ዓ.ም በባሕር ዳር ያደረገውን ስብሰባ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ነው ጥሪውን ያቀረበው።
"ከ12ኛ ክፍል አገር ዐቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ እየተነሳ ያለው ጥያቄ ከተማሪዎችና ወላጆች አልፎ የማህበረሰባችን ጥያቄ በመሆኑ አገር ዐቀፍ ፈተናዎች ድርጅት እና ትምህርት ሚኒስቴር አስቸኳይ እልባት እንዲሰጡት" ሲል ፓርቲው አሳስቧል።
"እስከዚያው ድረስ ግን የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንዲዘገይ በአጽንኦት እንጠይቃለን" ብሏል ፓርቲው በመግለጫው።
@minesterofeducation
>>Click here to continue<<