TG Telegram Group & Channel
መዓዛ ሠናይ | United States America (US)
Create: Update:

​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ከጌታችን ትንሣኤ በኋላ ያሉት ዕለታት ስያሜ

አሁደ፦

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሁድ ደቀ መዛርሙርቱ አይሁድን ፈርተው በተሰበሰቡበት ዝግ ቤቶ "ሰላም ለእናንተ ይሁን"ሌሎች ዳግም ስለ ተገለጠ  ዳግማይ ትንሳኤተብሏል ።

ሁለተኛ_ለምን_ተገለጠ?ተብሏል
💧◦ለሐዋርያው ቶማስ ትንሳኤውን ለማሳመን ።
የጌታችን ትንሳኤ ቶማስ ስለ ተጠራጠረ ጌታችን ቶማስ በተገኘበት ዝግ ቤት ተገልጦ ለቶማስ ና ወደኔ የተቸነከረውን እጄና ጉኔን ዳስስ ብሎታል ።
ቶማስም የተቸነከረው እጁን አይቶ የተወጋውን ጉኑ በእጁ ዳስሶ የጌታችን ትንሳኤ አምኗል ።ሃገረ ስብከቱም በሕንድ ስለ ነበረ ተጋድሎውም የፈጸመው እንዲሁም ሰማዕትነት የተቀበለው በሕንድ ነው ።
ያቺ የጌታችንን ጎን የነካች (የዳሰሰች)እጅ ሳትበሰብስ ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ተቀምጣለች ።እስካሁን ድረስ የሕንድ ሊቀ ጳጳስ ሲሾም በዛች እጅ ተመርጦና ተባርኮ እንደሚሾም አንዳንድ ሊቃውንት ይናገራሉ ።

💧◦ሰንበትን ሊያጸናልን ።
የአይሁድ ሰንበት፣እግዚአብሔር ሃያ ሁለትኘ ፍጥረታትን ፈጥሮ ያረፈባትና እረፉባት ብሎ ያዘዘን ሰንበት ቀዳም(ቅዳሜ)ናት ።

በሐዲስ ኪዳንም ጌታችን የተጸነሰባት ፣ከሙታን መካከል የተነሳባት፣አንዲሁም ደግሞ ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት(ዳግማይ ትንሳኤ)፣መንፈስ ቅዱስ የወረደባትና ሐዋርያት ከመጀመርያዋቹ ክርስቲያኖች ጋር በኅብረት ሆነው መንፈሳዊ ስራዋች የሚሰሩባት ቀን ዕለተ እሁድ ነበረች ።ቤተ ክርስቲያናችን ለቅዳሜ ቀዳሚት ሰንበት ለእሁድ ደግሞ ሰንበተ ክርስቲያን እያለች ለሁለቱም ቀናት እኩል ታከብራቸዋለች
።ጌታችንም ይቺ ቀን እረፍትነቷን ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት ቀን ናት ።እረፍት ስንልም ስራችንን ትተን ቁጭ ብለን (ተኝተን)የምናሳልፈው ማለት አይደለም ።እንደውም ከማንም ቀን በላይ አብዝተን መንፈሳዊ ስራዎች የምንሰራባቸው ቀናት ናቸው እንጂ ።
💧◦ምትሐት አለመሆኑ ለማስረዳት።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምትሐት እንዳልሆነና ቀድሞ የተዋሃደው ሥጋና መለኮት ፣ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑ ለማስረዳት ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦላቸዋል ።

በዝግ ቤት መግባቱ ደግሞ መለኮት እንዳልተለየውና ሥጋ ብቻው እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ።
"ብጹዓን እለ እንዘ ኢይሬእዩ የአምኑ"
(ዮሐ20:29)
አንድም
ዳግም ማለት ሁለተኛ ማለት ነው፡፡ ጌታ ሁለት ጊዜ አልተነሳም ፡፡ ዳግም የተባለው የትንሳኤው ስርዓት አና ቃለ እግዚአብሔር በዚህ ቀን ስለሚደገም ነው፡፡አንድም መነሳቱን ለአሥራ አንዱ ደቀመዛሙርት እንበለ ቶማስ ቢገልጥላቸው አምነው ለቶማስ ቢነግሩት የተቸነከሩ እግሮቹንና እጆቹን ካላየሁ ጣቴን በተወጋ ጎኑ ካላገባሁ
አላምንም ብሎ ነበርና በሳምንቱ ያምን ዘንድ ቶማስ ባለበት
ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው፡፡ ዮሐ ፳፥፳፮-ፍም

ቤተክርስቲያን ይህንን መገለጥ ዳግም ትንሳኤ ትለዋለች፡፡

፪፦ ፈጸምነ ይባላል
ይህ ስያሜ ደግሞ የፋሲካን በዓል አከበርን ስርዓቱን ዛሬ ፈጸምን ለማለት ነው፡፡
፫፦ አግብኦት ግብር ይባላል።
በዮሐ ፲፯፥፩ ጀምሮ በተገለጠው፡መፅሀፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት ጌታ " አባ ወአቡየ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ" ያለውን መዘምራን በቅዳሴ ማጠቃለያ አካባቢ ስለሚዘምሩበት ነው፡፡

ቶማስ ለምን ተጠራጠረ ?
መጠራጠሩ ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡
፩፦ሰዱቃዊ ስለነበረ፡፡ ሰዱቃውያን ደግሞ ትንሳኤ ሙታን የለም ብለው የሚጠራጠሩ ናቸውና ሳላይ አላምንም ብሎ
፪፦ ሌሎች ሐዋርያት ትንሳኤውን ሲሰብኩ ተነስቶ አይተነዋል ሲሉ እርሱ ደግሞ መነሳቱን ሰምቻለሁ ብሎ ማስተማር ስለሌለበት ለማየት ሳላይ አላምንም አለ።

ጌታ የተገለጠላቸው ደጆች ተዘግተው ሳሉ ነበር ፡፡ ዮሐ ፳፥፳፮ ገብቶ ሰላም አላችሁ አስታረቅኀችሁ አላቸው።

በተዘጋው ቤት እንዴት ገባ ?ተብሏል
💧ኤልሻዳይ ስለሆነ ፡፡ ዘፍ 17፥1 ሳራ ማሕጸኗ ተዘግቶ መውለድ ባልቻለች ጊዜ ልጅ የሰጣት ኤልሻዳይ ነው፡፡ ።

ሀና ፣ ኤልሳቤጥ ሌሎችም እንዲሁ፡፡ ሉቃ 1፥ 37 እስመ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር ፡፡ እንዲል ረቂቅ መለኮት ሥጋን እንደተዋሃደ ለማጠየቅ ፦ በተዘጋ ቤት ገባ፡፡

ዛሬም ደጆች ቢዘጉም ጌታ ይመጣል፡፡ብዙ ሰዎች በሕመም ተይዘው የመዳን ደጃቸው ተዘግቶ ሳለ ጌታ የመጣው ዮሐ
5፥3-12 ነፍሳት በዲያብሎስ ቁራኝነት ተይዘው ገነት ተዘግታ ሳለ ኢየሱስ መጥቶ የለ ? ሉቃ 2፥9

💧እስራኤላውያን የግብጽ ባርነት ቢያይልባቸው የነጻነት ደጃቸው ቢዘጋባቸውም ጌታ መጥቶ አድኗቸው የለ ? ዘጸ 3፥1-8

ሲወጡስ ከፊት ቀይ ባህር ከኀላ ፈርኦን ከቀኝና ግራ ገደልና ዳገት ቢገጥማቸውም አምላክ ደርሶላቸው የለ ? ዘጸ14፥1

💧ለሶስና (መ ሶስ 1፥1-23) ከውግረት አድኗት የለ?

💧ለአይሁድ / ዕብራውያን/ መ አስ 1-10 ሐማ ያሳወጀውን የሞት ፍርድ ቀይሮላቸው የለ?

💧ለሶስቱ ሕጻናት ት ዳን 3፥17 ከእሳት አውጥቷቸው የለ ?

💧ለሞተው አላዛር ዮሐ 11፥1-48 ከሞት አንስቶት የለ ?

ስለዚህ ሁሉን ቻዩ ጌታ ምን ደጅ ቢዘጋ መክፈት ይችላልና እንመነው ፡፡ እርሱን አምኖ ተስፋ ሚያደርግ አያፍርም መዝ 24፥3 ተብሎ ተጽፏልና ፡፡

ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

​​በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ከጌታችን ትንሣኤ በኋላ ያሉት ዕለታት ስያሜ

አሁደ፦

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሁድ ደቀ መዛርሙርቱ አይሁድን ፈርተው በተሰበሰቡበት ዝግ ቤቶ "ሰላም ለእናንተ ይሁን"ሌሎች ዳግም ስለ ተገለጠ  ዳግማይ ትንሳኤተብሏል ።

ሁለተኛ_ለምን_ተገለጠ?ተብሏል
💧◦ለሐዋርያው ቶማስ ትንሳኤውን ለማሳመን ።
የጌታችን ትንሳኤ ቶማስ ስለ ተጠራጠረ ጌታችን ቶማስ በተገኘበት ዝግ ቤት ተገልጦ ለቶማስ ና ወደኔ የተቸነከረውን እጄና ጉኔን ዳስስ ብሎታል ።
ቶማስም የተቸነከረው እጁን አይቶ የተወጋውን ጉኑ በእጁ ዳስሶ የጌታችን ትንሳኤ አምኗል ።ሃገረ ስብከቱም በሕንድ ስለ ነበረ ተጋድሎውም የፈጸመው እንዲሁም ሰማዕትነት የተቀበለው በሕንድ ነው ።
ያቺ የጌታችንን ጎን የነካች (የዳሰሰች)እጅ ሳትበሰብስ ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ተቀምጣለች ።እስካሁን ድረስ የሕንድ ሊቀ ጳጳስ ሲሾም በዛች እጅ ተመርጦና ተባርኮ እንደሚሾም አንዳንድ ሊቃውንት ይናገራሉ ።

💧◦ሰንበትን ሊያጸናልን ።
የአይሁድ ሰንበት፣እግዚአብሔር ሃያ ሁለትኘ ፍጥረታትን ፈጥሮ ያረፈባትና እረፉባት ብሎ ያዘዘን ሰንበት ቀዳም(ቅዳሜ)ናት ።

በሐዲስ ኪዳንም ጌታችን የተጸነሰባት ፣ከሙታን መካከል የተነሳባት፣አንዲሁም ደግሞ ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት(ዳግማይ ትንሳኤ)፣መንፈስ ቅዱስ የወረደባትና ሐዋርያት ከመጀመርያዋቹ ክርስቲያኖች ጋር በኅብረት ሆነው መንፈሳዊ ስራዋች የሚሰሩባት ቀን ዕለተ እሁድ ነበረች ።ቤተ ክርስቲያናችን ለቅዳሜ ቀዳሚት ሰንበት ለእሁድ ደግሞ ሰንበተ ክርስቲያን እያለች ለሁለቱም ቀናት እኩል ታከብራቸዋለች
።ጌታችንም ይቺ ቀን እረፍትነቷን ለማጽናት ሁለተኛ የተገለጠባት ቀን ናት ።እረፍት ስንልም ስራችንን ትተን ቁጭ ብለን (ተኝተን)የምናሳልፈው ማለት አይደለም ።እንደውም ከማንም ቀን በላይ አብዝተን መንፈሳዊ ስራዎች የምንሰራባቸው ቀናት ናቸው እንጂ ።
💧◦ምትሐት አለመሆኑ ለማስረዳት።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምትሐት እንዳልሆነና ቀድሞ የተዋሃደው ሥጋና መለኮት ፣ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑ ለማስረዳት ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦላቸዋል ።

በዝግ ቤት መግባቱ ደግሞ መለኮት እንዳልተለየውና ሥጋ ብቻው እንዳልሆነ ለማስረዳት ነው ።
"ብጹዓን እለ እንዘ ኢይሬእዩ የአምኑ"
(ዮሐ20:29)
አንድም
ዳግም ማለት ሁለተኛ ማለት ነው፡፡ ጌታ ሁለት ጊዜ አልተነሳም ፡፡ ዳግም የተባለው የትንሳኤው ስርዓት አና ቃለ እግዚአብሔር በዚህ ቀን ስለሚደገም ነው፡፡አንድም መነሳቱን ለአሥራ አንዱ ደቀመዛሙርት እንበለ ቶማስ ቢገልጥላቸው አምነው ለቶማስ ቢነግሩት የተቸነከሩ እግሮቹንና እጆቹን ካላየሁ ጣቴን በተወጋ ጎኑ ካላገባሁ
አላምንም ብሎ ነበርና በሳምንቱ ያምን ዘንድ ቶማስ ባለበት
ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው፡፡ ዮሐ ፳፥፳፮-ፍም

ቤተክርስቲያን ይህንን መገለጥ ዳግም ትንሳኤ ትለዋለች፡፡

፪፦ ፈጸምነ ይባላል
ይህ ስያሜ ደግሞ የፋሲካን በዓል አከበርን ስርዓቱን ዛሬ ፈጸምን ለማለት ነው፡፡
፫፦ አግብኦት ግብር ይባላል።
በዮሐ ፲፯፥፩ ጀምሮ በተገለጠው፡መፅሀፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት ጌታ " አባ ወአቡየ ግብረ ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ" ያለውን መዘምራን በቅዳሴ ማጠቃለያ አካባቢ ስለሚዘምሩበት ነው፡፡

ቶማስ ለምን ተጠራጠረ ?
መጠራጠሩ ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡
፩፦ሰዱቃዊ ስለነበረ፡፡ ሰዱቃውያን ደግሞ ትንሳኤ ሙታን የለም ብለው የሚጠራጠሩ ናቸውና ሳላይ አላምንም ብሎ
፪፦ ሌሎች ሐዋርያት ትንሳኤውን ሲሰብኩ ተነስቶ አይተነዋል ሲሉ እርሱ ደግሞ መነሳቱን ሰምቻለሁ ብሎ ማስተማር ስለሌለበት ለማየት ሳላይ አላምንም አለ።

ጌታ የተገለጠላቸው ደጆች ተዘግተው ሳሉ ነበር ፡፡ ዮሐ ፳፥፳፮ ገብቶ ሰላም አላችሁ አስታረቅኀችሁ አላቸው።

በተዘጋው ቤት እንዴት ገባ ?ተብሏል
💧ኤልሻዳይ ስለሆነ ፡፡ ዘፍ 17፥1 ሳራ ማሕጸኗ ተዘግቶ መውለድ ባልቻለች ጊዜ ልጅ የሰጣት ኤልሻዳይ ነው፡፡ ።

ሀና ፣ ኤልሳቤጥ ሌሎችም እንዲሁ፡፡ ሉቃ 1፥ 37 እስመ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር ፡፡ እንዲል ረቂቅ መለኮት ሥጋን እንደተዋሃደ ለማጠየቅ ፦ በተዘጋ ቤት ገባ፡፡

ዛሬም ደጆች ቢዘጉም ጌታ ይመጣል፡፡ብዙ ሰዎች በሕመም ተይዘው የመዳን ደጃቸው ተዘግቶ ሳለ ጌታ የመጣው ዮሐ
5፥3-12 ነፍሳት በዲያብሎስ ቁራኝነት ተይዘው ገነት ተዘግታ ሳለ ኢየሱስ መጥቶ የለ ? ሉቃ 2፥9

💧እስራኤላውያን የግብጽ ባርነት ቢያይልባቸው የነጻነት ደጃቸው ቢዘጋባቸውም ጌታ መጥቶ አድኗቸው የለ ? ዘጸ 3፥1-8

ሲወጡስ ከፊት ቀይ ባህር ከኀላ ፈርኦን ከቀኝና ግራ ገደልና ዳገት ቢገጥማቸውም አምላክ ደርሶላቸው የለ ? ዘጸ14፥1

💧ለሶስና (መ ሶስ 1፥1-23) ከውግረት አድኗት የለ?

💧ለአይሁድ / ዕብራውያን/ መ አስ 1-10 ሐማ ያሳወጀውን የሞት ፍርድ ቀይሮላቸው የለ?

💧ለሶስቱ ሕጻናት ት ዳን 3፥17 ከእሳት አውጥቷቸው የለ ?

💧ለሞተው አላዛር ዮሐ 11፥1-48 ከሞት አንስቶት የለ ?

ስለዚህ ሁሉን ቻዩ ጌታ ምን ደጅ ቢዘጋ መክፈት ይችላልና እንመነው ፡፡ እርሱን አምኖ ተስፋ ሚያደርግ አያፍርም መዝ 24፥3 ተብሎ ተጽፏልና ፡፡

ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን


>>Click here to continue<<

መዓዛ ሠናይ






Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)