TG Telegram Group & Channel
እልመስጦአግያ+++ | United States America (US)
Create: Update:

፩) ሴት ልጅ ወንዶች ባሉበት በዓውደ ምሕረት መዘመር አትችልም። ይህንን ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ነግሮናል።  1ኛ ቆሮ. ፲፬፣ ፴፬ "ሴቶችም በቤተክርስቲያን ዝም ይበሉ። ሊታዘዙ እንጂ ሊናገሩ አልተፈቀደምና። ኦሪትም እንዲህ ብሏልና። ለሴት በቤተክርስቲያን መናገር ክልክል ነው" እንዲል። በተጨማሪም 1ኛ ጢሞ. 2፣11 "ሴት ግን በጸጥታ ትኑር እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ እንድትሰለጥን አንፈቅድም" እንዲል። የሙሴ እኅት ማርያም እንኳ በሴቶች መካከል ዘመረች ይላል እንጂ በወንዶች መካከል አልዘመረችም። ዘጸ. ፲፭፣፳ "የአሮን እኅት ነቢይቱ ማርያምም ከበሮ በእጇ ወሰደች። ሴቶችም ሁሉ በከበሮና በዝማሬ በኋላዋ ወጡ። ማርያምም አስቀድማ ለእግዚአብሔር እንዘምር አለች" እንዲል። ሴት ሴቶችን ማስተማር ትችላለች። ቲቶ ፪፣፫ "ባልቴቶችም___በጎ የሆነውንም ትምህርት ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ለሴቶች ያስተምሩ" እንዲል። ሴቶች ዘማርያት ሆነው በዓውደ ምሕረት ሲዘምሩ ጳጳሱ ዝም ስላለ ልክ ነው አይባልም። ይህ በቸልተኝነት የመጣ ክፉ ልማድ ነው።
                            ።
ወደፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት፣ ከሥርዓት የተጣላ ትውልድ እንዳይፈጠር እሰጋለሁ። ምክንያቱም አሁን አሁን በተለይ ከ1900 ዓ. ም ወዲህ ብዙ ነገሮች ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጡ ናቸው። ልምድ ሆነው ሰውም ዝም ብሏል። ክፉ ልማድ ሥር ሳይሰድ ካልነቀልነው የወደፊት ምእመናን ሃይማኖታቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጠ እየመሰላቸው ይቸገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት የተጣሉ የልማድ ሰዎች ይሆኑብናል። በእርግጥ አንዳንድ ታላላቅ አድባራት ላይ አሁንም ቢሆን ሴቶች በዓውደ ምሕረት አይዘምሩም። ይህ በሁሉም ሊሆን ይገባል።
                                ።
፪) የጾም ሰዓት ከዐቢይ ጾም ውጭ ያሉት እስከ ፱ ሰዓት ይጾማሉ። ሰው ግን ጾሞ ግን 7 ሰዓት ላይ ይበላል። ከየት የመጣ ሥርዓት ነው ይሄ??? ጾሙን ሳይጨርሰው ገደፈኮ?። ይህ ሊስተካከል ይገባል።
                                ።
አንድ ቀን ቆማ ፋሲለደስ አቡነ እንድርያስ ዐቢይ ጾም ሊገባ ሲል ዘወረደ እስከ ፲፪ ሰዓት ይጾማል፣ ሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ ፩ ሰዓት ይጾማል። ከቅድስት እስከ ኒቆዲሞስ ዓርብ እስከ ፲፩ ሰዓት ይጾማል ብለው አስተማሩና እንኳን እውነቱን ነገርኳችሁ እንጂ ከዚህ በኋላ የራሳችሁ ውሳኔ ነው አሉ።
                                ።
እና ብዙ እውነታዎች አሉ። ያው መረር ቢላችሁም እውነታዋን መናገር ይሻላል። አንዳንዱ ይህ አንገብጋቢ ጉዳይ አይደለም ይልሀል። የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ካለመጠበቅ በላይ አንገብጋቢ ጉዳይ አለ ?

፩) ሴት ልጅ ወንዶች ባሉበት በዓውደ ምሕረት መዘመር አትችልም። ይህንን ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ነግሮናል።  1ኛ ቆሮ. ፲፬፣ ፴፬ "ሴቶችም በቤተክርስቲያን ዝም ይበሉ። ሊታዘዙ እንጂ ሊናገሩ አልተፈቀደምና። ኦሪትም እንዲህ ብሏልና። ለሴት በቤተክርስቲያን መናገር ክልክል ነው" እንዲል። በተጨማሪም 1ኛ ጢሞ. 2፣11 "ሴት ግን በጸጥታ ትኑር እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ እንድትሰለጥን አንፈቅድም" እንዲል። የሙሴ እኅት ማርያም እንኳ በሴቶች መካከል ዘመረች ይላል እንጂ በወንዶች መካከል አልዘመረችም። ዘጸ. ፲፭፣፳ "የአሮን እኅት ነቢይቱ ማርያምም ከበሮ በእጇ ወሰደች። ሴቶችም ሁሉ በከበሮና በዝማሬ በኋላዋ ወጡ። ማርያምም አስቀድማ ለእግዚአብሔር እንዘምር አለች" እንዲል። ሴት ሴቶችን ማስተማር ትችላለች። ቲቶ ፪፣፫ "ባልቴቶችም___በጎ የሆነውንም ትምህርት ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ለሴቶች ያስተምሩ" እንዲል። ሴቶች ዘማርያት ሆነው በዓውደ ምሕረት ሲዘምሩ ጳጳሱ ዝም ስላለ ልክ ነው አይባልም። ይህ በቸልተኝነት የመጣ ክፉ ልማድ ነው።
                            ።
ወደፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት፣ ከሥርዓት የተጣላ ትውልድ እንዳይፈጠር እሰጋለሁ። ምክንያቱም አሁን አሁን በተለይ ከ1900 ዓ. ም ወዲህ ብዙ ነገሮች ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጡ ናቸው። ልምድ ሆነው ሰውም ዝም ብሏል። ክፉ ልማድ ሥር ሳይሰድ ካልነቀልነው የወደፊት ምእመናን ሃይማኖታቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ያፈነገጠ እየመሰላቸው ይቸገራሉ። ከመጽሐፍ ቅዱስ፣ ከፍትሐ ነገሥት የተጣሉ የልማድ ሰዎች ይሆኑብናል። በእርግጥ አንዳንድ ታላላቅ አድባራት ላይ አሁንም ቢሆን ሴቶች በዓውደ ምሕረት አይዘምሩም። ይህ በሁሉም ሊሆን ይገባል።
                                ።
፪) የጾም ሰዓት ከዐቢይ ጾም ውጭ ያሉት እስከ ፱ ሰዓት ይጾማሉ። ሰው ግን ጾሞ ግን 7 ሰዓት ላይ ይበላል። ከየት የመጣ ሥርዓት ነው ይሄ??? ጾሙን ሳይጨርሰው ገደፈኮ?። ይህ ሊስተካከል ይገባል።
                                ።
አንድ ቀን ቆማ ፋሲለደስ አቡነ እንድርያስ ዐቢይ ጾም ሊገባ ሲል ዘወረደ እስከ ፲፪ ሰዓት ይጾማል፣ ሰሙነ ሕማማት እስከ ምሽቱ ፩ ሰዓት ይጾማል። ከቅድስት እስከ ኒቆዲሞስ ዓርብ እስከ ፲፩ ሰዓት ይጾማል ብለው አስተማሩና እንኳን እውነቱን ነገርኳችሁ እንጂ ከዚህ በኋላ የራሳችሁ ውሳኔ ነው አሉ።
                                ።
እና ብዙ እውነታዎች አሉ። ያው መረር ቢላችሁም እውነታዋን መናገር ይሻላል። አንዳንዱ ይህ አንገብጋቢ ጉዳይ አይደለም ይልሀል። የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ካለመጠበቅ በላይ አንገብጋቢ ጉዳይ አለ ?


>>Click here to continue<<

እልመስጦአግያ+++




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)