TG Telegram Group & Channel
እልመስጦአግያ+++ | United States America (US)
Create: Update:

እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነውና እሱ ያደረገው ተአምር ምንም ቢሆን ከከሃሊነቱ አንጻር የሚጠበቅ ነገር ነው፡፡ ለደካማው የሰው ልጅ ኃይል ሠጥቶ የሚሠራውን ነገር ስንሰማ ግን ኃይሉ በሰው ድካም ሲገለጥ ስናይ የበለጠ እናደንቃለን፡፡ የቅዱሳን ተአምር መቼም ቢደረግ በእግዚአብሔር እጅ የተደረገ ነው፡፡ ‘ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳችስ እንኳን ያለ እርሱ አልሆነም’ እንደሚል ድንግል ማርያም ያደረገችው ተአምር ሁሉ በእርሱ የተደረገ ነው፡፡ ተአምረ ማርያምም ራሱ ተአምረ ኢየሱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተአምር ይሠራል ፤ ያለ ድንግል ማርያምም ተአምር ሊያደርግ ይችላል፡፡ ድንግል ማርያም ግን ያለ እግዚአብሔር አንዳች ተአምር ልትሠራ አትችልም፡፡ ክርስቶስ ‘ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም’ ያለው ለዚህ ነው፡፡ (ዮሐ. 15፡5)

ኦርቶዶክሳዊያን ስለ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክዋን ፣ ዘለዓለማዊ ድንግልዋን ፣ መቼም መች መርገም ያልደረሰባት ንጽሕት መሆንዋ ፣ አማላጅነትዋን እናምናለን ፤ ከዚህ ፈቀቅ ሊያደርገን የሚሻ ቢኖርም እነዚህ የነገረ ማርያም መሠረተ እምነቶቻችን ናቸውና እስከ ሰማዕትነት ድረስ እንጸናለን፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ‘እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል’ ‘የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም’ ብሎ ተናግሯል፡፡ (ዮሐ. 12፡14 ፤ ማቴ. 17፡20) ስለዚህ ‘ያመነች ብፅዕት’ የተባለችው ድንግል ማርያም (ሉቃ. 1፡45) በልጅዋ አነጋገር ክርስቶስ የሚያደርገውን ተአምር ታደርጋለች ፣ ከዚያም የሚበልጥ ታደርጋለች ፣ የሚሳናትም የለም፡፡

ተአምራትን የሚያነብ ሰው በእምነት ካላነበበው ብዙ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ እውነት ለመናገር ይህ ከክህደት የተነሣ ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊነት ደረጃችን ዝቅ በማለታችን የተነሣ የሚፈጠር ችግር ነው፡፡ በተአምራት መጻሕፍት ላይ ተደረጉ የሚባሉ ተአምራትን በእርግጠኝነት የሚያምን ልብ ቢኖረን ኖሮ ተአምራቱን እኛ ራሳችን ልንፈጽማቸው በቻልን ነበር፡፡ እኛ ግን እንኳንስ ተአምራቱን ልንፈጽማቸው ቀርቶ ተፈጽመዋል ብለን አምነን ለመቀበልም እንኳን ገና ነን፡፡ በዚህ የተነሣ የቅዱሳን ተአምራት ሲነበቡ ልባችን በጥርጣሬ ይናወጻል፡፡ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ደግሞ ተአምራት ሲሰሙ ‘አቤት ተረት’ ለማለት ተነቦ እስከሚያልቅ ድረስ አይጠብቁም፡፡

በገድላትና ድርሳናት ላይ ያሉ ታሪኮችንና ተአምራትን ተረታ ተረት ናቸው ብሎ ለመደምደም ከቸኮልክ መጽሐፍ ቅዱስንም ማመንህ አስገራሚ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስም ብዙ ለማመን የሚከብዱ ታሪኮች አሉበት፡፡ እባብ ከሰው ጋር ሲነጋገር ፣ አህያ ጌታዋን ስትመክር ፣ ኤልያስ ዝናብን እንደ ቧንቧ ውኃ ሲከፍትና ሲዘጋ ፣ ቁራ አስተናጋጅ ሲሆን ፣ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ሲሳፈር ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሲጸልይ ፣ የኤልሳዕ አጥንት ሙት ሲያስነሳ ፣ የኤልያስ ልብስ ባሕር ሲከፍል ፣ የሙሴ በትር እባብ ሲሆን ፣ ጌታ በምራቁ ዓይን ሲፈጥር ፣ የአራት ቀን ሬሳ በስም ተጠርቶ ሲወጣ ፣ የጴጥሮስ ጥላ ሲፈውስ ፣ የጳውሎስ ጨርቅ ሙት ሲያስነሣ ተጽፎ ታገኛለህ፡፡ ይሄንን ሁሉ እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ ይችላል ብለህ በእምነት ካልተቀበልከው በስተቀር እንዴት ታደርገዋለህ? አንድ አባት ‘ዮናስን አሣ አንበሪ ዋጠው የሚለውን ታሪክ እንዴት ማመን ይቻላል?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘የምናወራው ስለ እግዚአብሔር ከሆነ እንኳንስ ዓሣ አንበሪው ዮናስን ዋጠው ተብሎ ይቅርና ዮናስ ዓሣ አንበሪውን ዋጠው ቢባልም አምናለሁ’ ብለዋል፡፡ ‘አይ ይኼ እኮ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈ ነው’ ካልከኝ እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ሲጠናቀቅ ሥራ አቁሞአል ማለት ነው? ‘እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ’ ሲል አብረን አልሰማነውም? (ማቴ. 28፡19)

ወደ ተአምረ ማርያም እንመለስና ለመሆኑ ተአምረ ማርያምን ማን ጻፈው? ከየት መጣ? ተአምረ ማርያም ላይ የሚነሡ ብዙ ጥያቄዎች ሁሉም የተሳሳቱ ናቸው ሊባል ይችላል? ብፁዓን አባቶች "ተአምረ ማርያም ላይ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ሥራዎች እየተሠሩ ነው" ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? በቤተ ክርስቲያንዋ በኩልስ በአዋልድ መጻሕፍት ዙሪያ የሚነሡ ጉዳዮች የሉም? ሌሎች የሚያሳዩት ንቀትና ስድብ እንዳለ ሆኖ በአዋልድ በቤተ ክርስቲያንዋ እይታስ ምን እየተሠራ ነው? የዚህ ጽሑፍ ቀጣይ ክፍል ትኩረት ይሆናል፡፡

ክፍል ሁለት - ይቀጥላል
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 12 2015 ዓ.ም.

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ ነውና እሱ ያደረገው ተአምር ምንም ቢሆን ከከሃሊነቱ አንጻር የሚጠበቅ ነገር ነው፡፡ ለደካማው የሰው ልጅ ኃይል ሠጥቶ የሚሠራውን ነገር ስንሰማ ግን ኃይሉ በሰው ድካም ሲገለጥ ስናይ የበለጠ እናደንቃለን፡፡ የቅዱሳን ተአምር መቼም ቢደረግ በእግዚአብሔር እጅ የተደረገ ነው፡፡ ‘ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳችስ እንኳን ያለ እርሱ አልሆነም’ እንደሚል ድንግል ማርያም ያደረገችው ተአምር ሁሉ በእርሱ የተደረገ ነው፡፡ ተአምረ ማርያምም ራሱ ተአምረ ኢየሱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተአምር ይሠራል ፤ ያለ ድንግል ማርያምም ተአምር ሊያደርግ ይችላል፡፡ ድንግል ማርያም ግን ያለ እግዚአብሔር አንዳች ተአምር ልትሠራ አትችልም፡፡ ክርስቶስ ‘ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም’ ያለው ለዚህ ነው፡፡ (ዮሐ. 15፡5)

ኦርቶዶክሳዊያን ስለ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክዋን ፣ ዘለዓለማዊ ድንግልዋን ፣ መቼም መች መርገም ያልደረሰባት ንጽሕት መሆንዋ ፣ አማላጅነትዋን እናምናለን ፤ ከዚህ ፈቀቅ ሊያደርገን የሚሻ ቢኖርም እነዚህ የነገረ ማርያም መሠረተ እምነቶቻችን ናቸውና እስከ ሰማዕትነት ድረስ እንጸናለን፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ‘እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል’ ‘የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም’ ብሎ ተናግሯል፡፡ (ዮሐ. 12፡14 ፤ ማቴ. 17፡20) ስለዚህ ‘ያመነች ብፅዕት’ የተባለችው ድንግል ማርያም (ሉቃ. 1፡45) በልጅዋ አነጋገር ክርስቶስ የሚያደርገውን ተአምር ታደርጋለች ፣ ከዚያም የሚበልጥ ታደርጋለች ፣ የሚሳናትም የለም፡፡

ተአምራትን የሚያነብ ሰው በእምነት ካላነበበው ብዙ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ እውነት ለመናገር ይህ ከክህደት የተነሣ ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊነት ደረጃችን ዝቅ በማለታችን የተነሣ የሚፈጠር ችግር ነው፡፡ በተአምራት መጻሕፍት ላይ ተደረጉ የሚባሉ ተአምራትን በእርግጠኝነት የሚያምን ልብ ቢኖረን ኖሮ ተአምራቱን እኛ ራሳችን ልንፈጽማቸው በቻልን ነበር፡፡ እኛ ግን እንኳንስ ተአምራቱን ልንፈጽማቸው ቀርቶ ተፈጽመዋል ብለን አምነን ለመቀበልም እንኳን ገና ነን፡፡ በዚህ የተነሣ የቅዱሳን ተአምራት ሲነበቡ ልባችን በጥርጣሬ ይናወጻል፡፡ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ደግሞ ተአምራት ሲሰሙ ‘አቤት ተረት’ ለማለት ተነቦ እስከሚያልቅ ድረስ አይጠብቁም፡፡

በገድላትና ድርሳናት ላይ ያሉ ታሪኮችንና ተአምራትን ተረታ ተረት ናቸው ብሎ ለመደምደም ከቸኮልክ መጽሐፍ ቅዱስንም ማመንህ አስገራሚ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስም ብዙ ለማመን የሚከብዱ ታሪኮች አሉበት፡፡ እባብ ከሰው ጋር ሲነጋገር ፣ አህያ ጌታዋን ስትመክር ፣ ኤልያስ ዝናብን እንደ ቧንቧ ውኃ ሲከፍትና ሲዘጋ ፣ ቁራ አስተናጋጅ ሲሆን ፣ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ሲሳፈር ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሲጸልይ ፣ የኤልሳዕ አጥንት ሙት ሲያስነሳ ፣ የኤልያስ ልብስ ባሕር ሲከፍል ፣ የሙሴ በትር እባብ ሲሆን ፣ ጌታ በምራቁ ዓይን ሲፈጥር ፣ የአራት ቀን ሬሳ በስም ተጠርቶ ሲወጣ ፣ የጴጥሮስ ጥላ ሲፈውስ ፣ የጳውሎስ ጨርቅ ሙት ሲያስነሣ ተጽፎ ታገኛለህ፡፡ ይሄንን ሁሉ እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ ይችላል ብለህ በእምነት ካልተቀበልከው በስተቀር እንዴት ታደርገዋለህ? አንድ አባት ‘ዮናስን አሣ አንበሪ ዋጠው የሚለውን ታሪክ እንዴት ማመን ይቻላል?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘የምናወራው ስለ እግዚአብሔር ከሆነ እንኳንስ ዓሣ አንበሪው ዮናስን ዋጠው ተብሎ ይቅርና ዮናስ ዓሣ አንበሪውን ዋጠው ቢባልም አምናለሁ’ ብለዋል፡፡ ‘አይ ይኼ እኮ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈ ነው’ ካልከኝ እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ሲጠናቀቅ ሥራ አቁሞአል ማለት ነው? ‘እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ’ ሲል አብረን አልሰማነውም? (ማቴ. 28፡19)

ወደ ተአምረ ማርያም እንመለስና ለመሆኑ ተአምረ ማርያምን ማን ጻፈው? ከየት መጣ? ተአምረ ማርያም ላይ የሚነሡ ብዙ ጥያቄዎች ሁሉም የተሳሳቱ ናቸው ሊባል ይችላል? ብፁዓን አባቶች "ተአምረ ማርያም ላይ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ሥራዎች እየተሠሩ ነው" ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? በቤተ ክርስቲያንዋ በኩልስ በአዋልድ መጻሕፍት ዙሪያ የሚነሡ ጉዳዮች የሉም? ሌሎች የሚያሳዩት ንቀትና ስድብ እንዳለ ሆኖ በአዋልድ በቤተ ክርስቲያንዋ እይታስ ምን እየተሠራ ነው? የዚህ ጽሑፍ ቀጣይ ክፍል ትኩረት ይሆናል፡፡

ክፍል ሁለት - ይቀጥላል
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 12 2015 ዓ.ም.

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)


>>Click here to continue<<

እልመስጦአግያ+++




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)