TG Telegram Group & Channel
እልመስጦአግያ+++ | United States America (US)
Create: Update:

በአጭሩ ዓረፍተ ነገሩ ሥጋ ወደሙን ዘወትር በመቀበል ሕይወት የሚኖርን ክርስቲያን የሚመለከት ቃል ነው፡፡ ይህ ክርስቲያን ፍጹም መንፈሳዊ ሕይወትን እየኖረ እንዳለ ምስክር የሚሆነው ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የሚከለክለው ደዌ ወይም የታወቀ ምክንያት እንጂ አልቆርብም የሚል የኃጢአት ሰበብ አይደለም፡፡ እንዲህ ላለው ትጉሕ ቆራቢ ሰው ሁልጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየገሠገሠ መቁረብ ልማዱ ነውና አስቀድሶ አለመቁረብም ኀዘን ይሆንበታል፡፡ ለዚህ ሰው መቅድመ ተአምረ ማርያም ያጽናናዋል፡፡ ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ሕመም ስለከለከለህ ባለመቁረብህ አትዘን ቢያንስ ተአምርዋን ሰምተህ ሒድ ፤ በዚያ ዕለት ልትቆርብ ተመኝተሃልና ሰምተህ በመሔድህ ያን ቀን ብትቆርብ የምታገኘውን በረከት አላስቀርብህም’ ነው፡፡ ይህ ግን ንስሓ አልገባም አልቆርብም ተአምርዋን ሰምቼ ይበቃኛል የሚል ብልጣ ብልጥ ትዕቢተኛ ሰው የሚሠራ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህንን ዓይነቱን ሰው ከመቁረብ የሚከለክለው ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ደዌ ሳይሆን’ የኃጢአት ፍቅር ነው፡፡

ሦስተኛው ጥያቄ ‘ለሥዕልዋ ያልሰገደ ከቆመበት ቦታ ይጥፋ የሚል እርግማን እንዴት በሐዲስ ኪዳን ይነገራል?’ ነው፡፡ ‘ለሥዕልዋ ስገዱ’ ማለት ለድንግል ማርያም ስገዱ ማለት ነው እንጂ እርስዋና ሥዕልዋን ነጣጥሎ ለማየት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ በእንተ ሥዕላት አምላካዊያት (On the Divine Images) ላይ ደጋግሞ እንደገለጸው በሥዕላት ፊት የሚደረግ ማንኛውም አክብሮትና ስግደት ለሥዕሉ ሳይሆን ለሥዕሉ ባለቤት ነው፡፡ ድርሳነ ሚካኤልም ‘ወሶበ ንሰግድ ቅድመ ሥዕላት አምላካዊያት አኮ ዘንሰግድ ለረቅ ወለቀለም ወለግብረ ዕድ’ ‘በእግዚአብሔር ሥዕል በተሳሉ በአምላካዊያት ሥዕላት ፊት ስንሰግድ የምንሰግደው ለወረቀቱ ለቀለሙ ወይንም ለሰው የእጅ ሥራ አይደለም’ ስግደትና ሥዕላትን በሚመለከት እነዚህን ቀደምት ጽሑፎች ይመልከቱ፡፡

‘በሐዲስ ኪዳን እንዴት እርግማን እንሰማለን’ የሚለው ተቃውሞ ‘እንዲህ የሚያደርግ መንፈስ የተወጋ ይሁን’ ‘ወግቼዋለሁ’ ሲሉ ከሚውሉ ሰዎች አቅጣጫ መነሣቱ አሁንም አስደናቂ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ ጉዳዩ የሚረገመው አካልና እርግማኑ ተገቢነት ላይ እንወያይ እንጂ ሐዲስ ኪዳን ላይ ጨርሶ የግዝት ቃል ሥራ አቁሞአል ማለት አይቻልም፡፡ ጌታ በለስዋን ‘ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ብሏታል’ /ማቴ. 21፡19/ ሐዋርያት ‘ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን’ ‘ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን’ ብለዋል፡፡ /ገላ.1፡8፣9/ እግዚአብሔር አያሰማን እንጂ በዕለተ ምጽአትም ‘እናንተ ርጉማን’ የሚለው ቃል የመጨረሻው ቃል ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ቃል ተራ እርግማን ሳይሆን በድርጊቱ የተገኙትን ከክርስትና ኅብረት የሚለይ በምድር ያሰረችው በሰማይ የታሰረ የሚሆንላት ቤተ ክርስቲያን የምትናገረው ቃለ ውግዘት (በግሪኩ Anathema) ነው፡፡ ይህም በተስፋ የምንጠብቃት መንግሥተ ሰማያት እስክትመጣና ‘ከእንግዲህ ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም፡፡ የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል ባሪያዎቹም ያመልኩታል ፊቱንም ያያሉ’ የሚለው ቃል እስከሚፈጸምልን ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ (ራእ. 22፡3)

የመጨረሻው ነጥብ ‘የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም እንጂ 16ቱን ትእዛዛት በመጠበቅ አይደለም እንዴት ይባላል?’ የሚለው ነው፡፡ መደጋገም ይሆንብኛል እንጂ አሁንም ጥያቄው ከእነርሱ መነሣቱ ያስደንቀኛል፡፡ ፕሮቴስታንቲዝም የትእዛዛት ተቆርቋሪ መሆን የጀመረው ከመቼ ወዲህ ነው? በማመን እንጂ ትእዛዝ በመጠበቅ አይዳንም በሚለው ትምህርት ምክንያት ስንት ውዝግብ አልተነሣም? ጳውሎስ የመገረዝን ሕግ ሥራ ለአሕዛብ ጽድቅ የግድ አስፈላጊ አይደለም ብሎ ያስተማረበትን ሮሜና ገላትያ ያለ አገባቡ በአጠቃላይ በጎ ሥራ አያፈልግም እንዳለ አድርገው በያዙት የተሳሳተ መረዳት ምክንያት በሰማይ በክብር አብረው የሚዘምሩትን ጳውሎስና ያዕቆብን ሳይጣሉ ያጣሏቸው እነርሱ አይደሉምን? አሁን ደግሞ ተአምረ ማርያምን ጎዳን ብለው እንዴት ትእዛዝ መፈጸም አያስፈልግም ትላላችሁ? ብለው ሲመጡ ማየት ምንኛ አስገራሚ ነው?

በመሠረቱ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እነሱ እንደሚሉት ሥራ ብቻውን ያጸድቃል ብላ አምና አታውቅም፡፡ ልጆችዋንም እኔ በጎ ሥራ አለኝ በእርሱ እጸድቃለሁ ብለው እንዳያስቡ ታስጠነቅቃለች፡፡ ጸሎትዋም መዝሙርዋም ‘ምግባር የለኝም’ ነው፡፡ ‘እንበለ ምግባር ተራድእኒ ፍጡነ ፤ ምግባርየሰ ኃጢአተ ኮነ’ ‘እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ ፤ ቦኑ በከንቱ ኪዳንኪ ኮነ’ ‘በምን ምግባሬ ፊትሽን አየዋለሁ’ ‘እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኜያለሁ’ ወዘተ የሚሉት እልፍ ምስጋናዎች ቤተ ክርስቲያን ልጆችዋ በምግባሬ እጸድቃለሁ ብለው ተስፋ እንዳያደርጉና በክርስቶስ በማመናቸው (በሥጋ እንደመጣና ከድንግል ማርያም እንደተወለደ ማመንን ይጨምራል) እና በእግዚአብሔር ጸጋ ወይም ቸርነት እንደሚጸድቁ (እምነት + ሥራ + ጸጋ) ታስተምራለች፡፡

የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም መባሉ የሚያበሳጨው ካለ መጽሐፍ ቅዱስ ‘ነገር ግን በፍቅር እርስ በእርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ’ ይላል፡፡ ገላ. 5፡13 እንኳንስ ለአምላክ እናት አጠገብህ ላለው ወንድምህም በፍቅር ባሪያ ብትሆን ትጠቀማለህ እንጂ አትጎዳም፡፡ ለድንግል ማርያም ባሪያዋና ታዛዥዋ ብትሆን ግን ብዙ ትጠቀማለህ፡፡ ክርስቲያኖች ሆይ ልንገራችሁ ሁሉን ትታችሁ ለድንግል ማርያም ብቻ ታዘዙ፡፡ የእርስዋ ትእዛዝ አንድ ነው ‘የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ’ ዮሐ. 2፡5


+ ተአምራትን እንዴት እናያቸዋለን? +

መጽሐፍ ቅዱስ ‘የሐዋርያት ሥራ’ን የመሰሉ ሰዎች በእግዚአብሔር ኃይል የሠሩትን ሥራ የሚተርኩ መጻሕፍት ያለበት መጽሐፍ ነው፡፡ ‘የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሏቸው’ በማለት ሕያዋን መጽሐፍት ወይም ተንቀሳቃሽ መጽሐፍ ቅዱስ /Living bible or moving bible/ ተብለው የሚጠሩትን የቅዱሳንን ሕይወት እንድናጠና እና በኑሮአቸው እንድንመስላቸው ያሳስበናል፡፡ (ዕብ. 13፡7) ቅዱስ ጳውሎስ ‘እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ’ ብሎ እንደነገረን ክርስቶስን ለመምሰል የጳውሎስን የሕይወት ታሪክ ማጥናት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ (1ቆሮ. 11፡1) ራሱ ጳውሎስም ከእርሱ የቀደሙ የእምነት አርበኞችን አስደናቂ ታሪክ ከዘረዘረ በኋላ ‘ሁሉን እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል’ ብሏል፡፡ (ዕብ. 11፡32) ጳውሎስ የቅዱሳኑን ታሪክ ለመተረክ ያጠረው ጊዜ እንጂ ፍቅር አልነበረም፡፡

እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ ያደረገውን መስማትም የቅዱሳን ታሪክ አካል ነው፡፡ ‘በሐዋርያት እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ’ ‘እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር’ እንደሚል እግዚአብሔር በባሪያዎቹ እጅ ታላላቅ ተአምራት ያደርጋል፡፡ (ሐዋ. 2፡42 ፣ 19፡11) የእስራኤል ንጉሥ ‘ኤልሳዕ ያደረገውን ተአምር እስቲ ንገረኝ’ እያለ ግያዝን እየጠየቀ በደስታ ይሰማ እንደነበረ የእግዚአብሔር ቅዱሳን ያደረጉትን ተአምር መስማት ለምናምን ሰዎች እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው፡፡ (2ነገሥ. 8፡4)

በአጭሩ ዓረፍተ ነገሩ ሥጋ ወደሙን ዘወትር በመቀበል ሕይወት የሚኖርን ክርስቲያን የሚመለከት ቃል ነው፡፡ ይህ ክርስቲያን ፍጹም መንፈሳዊ ሕይወትን እየኖረ እንዳለ ምስክር የሚሆነው ሥጋ ወደሙን ከመቀበል የሚከለክለው ደዌ ወይም የታወቀ ምክንያት እንጂ አልቆርብም የሚል የኃጢአት ሰበብ አይደለም፡፡ እንዲህ ላለው ትጉሕ ቆራቢ ሰው ሁልጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየገሠገሠ መቁረብ ልማዱ ነውና አስቀድሶ አለመቁረብም ኀዘን ይሆንበታል፡፡ ለዚህ ሰው መቅድመ ተአምረ ማርያም ያጽናናዋል፡፡ ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ሕመም ስለከለከለህ ባለመቁረብህ አትዘን ቢያንስ ተአምርዋን ሰምተህ ሒድ ፤ በዚያ ዕለት ልትቆርብ ተመኝተሃልና ሰምተህ በመሔድህ ያን ቀን ብትቆርብ የምታገኘውን በረከት አላስቀርብህም’ ነው፡፡ ይህ ግን ንስሓ አልገባም አልቆርብም ተአምርዋን ሰምቼ ይበቃኛል የሚል ብልጣ ብልጥ ትዕቢተኛ ሰው የሚሠራ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህንን ዓይነቱን ሰው ከመቁረብ የሚከለክለው ‘የታወቀ ምክንያት ወይም ደዌ ሳይሆን’ የኃጢአት ፍቅር ነው፡፡

ሦስተኛው ጥያቄ ‘ለሥዕልዋ ያልሰገደ ከቆመበት ቦታ ይጥፋ የሚል እርግማን እንዴት በሐዲስ ኪዳን ይነገራል?’ ነው፡፡ ‘ለሥዕልዋ ስገዱ’ ማለት ለድንግል ማርያም ስገዱ ማለት ነው እንጂ እርስዋና ሥዕልዋን ነጣጥሎ ለማየት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ በእንተ ሥዕላት አምላካዊያት (On the Divine Images) ላይ ደጋግሞ እንደገለጸው በሥዕላት ፊት የሚደረግ ማንኛውም አክብሮትና ስግደት ለሥዕሉ ሳይሆን ለሥዕሉ ባለቤት ነው፡፡ ድርሳነ ሚካኤልም ‘ወሶበ ንሰግድ ቅድመ ሥዕላት አምላካዊያት አኮ ዘንሰግድ ለረቅ ወለቀለም ወለግብረ ዕድ’ ‘በእግዚአብሔር ሥዕል በተሳሉ በአምላካዊያት ሥዕላት ፊት ስንሰግድ የምንሰግደው ለወረቀቱ ለቀለሙ ወይንም ለሰው የእጅ ሥራ አይደለም’ ስግደትና ሥዕላትን በሚመለከት እነዚህን ቀደምት ጽሑፎች ይመልከቱ፡፡

‘በሐዲስ ኪዳን እንዴት እርግማን እንሰማለን’ የሚለው ተቃውሞ ‘እንዲህ የሚያደርግ መንፈስ የተወጋ ይሁን’ ‘ወግቼዋለሁ’ ሲሉ ከሚውሉ ሰዎች አቅጣጫ መነሣቱ አሁንም አስደናቂ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ ጉዳዩ የሚረገመው አካልና እርግማኑ ተገቢነት ላይ እንወያይ እንጂ ሐዲስ ኪዳን ላይ ጨርሶ የግዝት ቃል ሥራ አቁሞአል ማለት አይቻልም፡፡ ጌታ በለስዋን ‘ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ብሏታል’ /ማቴ. 21፡19/ ሐዋርያት ‘ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን’ ‘ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን’ ብለዋል፡፡ /ገላ.1፡8፣9/ እግዚአብሔር አያሰማን እንጂ በዕለተ ምጽአትም ‘እናንተ ርጉማን’ የሚለው ቃል የመጨረሻው ቃል ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ቃል ተራ እርግማን ሳይሆን በድርጊቱ የተገኙትን ከክርስትና ኅብረት የሚለይ በምድር ያሰረችው በሰማይ የታሰረ የሚሆንላት ቤተ ክርስቲያን የምትናገረው ቃለ ውግዘት (በግሪኩ Anathema) ነው፡፡ ይህም በተስፋ የምንጠብቃት መንግሥተ ሰማያት እስክትመጣና ‘ከእንግዲህ ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም፡፡ የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል ባሪያዎቹም ያመልኩታል ፊቱንም ያያሉ’ የሚለው ቃል እስከሚፈጸምልን ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ (ራእ. 22፡3)

የመጨረሻው ነጥብ ‘የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም እንጂ 16ቱን ትእዛዛት በመጠበቅ አይደለም እንዴት ይባላል?’ የሚለው ነው፡፡ መደጋገም ይሆንብኛል እንጂ አሁንም ጥያቄው ከእነርሱ መነሣቱ ያስደንቀኛል፡፡ ፕሮቴስታንቲዝም የትእዛዛት ተቆርቋሪ መሆን የጀመረው ከመቼ ወዲህ ነው? በማመን እንጂ ትእዛዝ በመጠበቅ አይዳንም በሚለው ትምህርት ምክንያት ስንት ውዝግብ አልተነሣም? ጳውሎስ የመገረዝን ሕግ ሥራ ለአሕዛብ ጽድቅ የግድ አስፈላጊ አይደለም ብሎ ያስተማረበትን ሮሜና ገላትያ ያለ አገባቡ በአጠቃላይ በጎ ሥራ አያፈልግም እንዳለ አድርገው በያዙት የተሳሳተ መረዳት ምክንያት በሰማይ በክብር አብረው የሚዘምሩትን ጳውሎስና ያዕቆብን ሳይጣሉ ያጣሏቸው እነርሱ አይደሉምን? አሁን ደግሞ ተአምረ ማርያምን ጎዳን ብለው እንዴት ትእዛዝ መፈጸም አያስፈልግም ትላላችሁ? ብለው ሲመጡ ማየት ምንኛ አስገራሚ ነው?

በመሠረቱ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እነሱ እንደሚሉት ሥራ ብቻውን ያጸድቃል ብላ አምና አታውቅም፡፡ ልጆችዋንም እኔ በጎ ሥራ አለኝ በእርሱ እጸድቃለሁ ብለው እንዳያስቡ ታስጠነቅቃለች፡፡ ጸሎትዋም መዝሙርዋም ‘ምግባር የለኝም’ ነው፡፡ ‘እንበለ ምግባር ተራድእኒ ፍጡነ ፤ ምግባርየሰ ኃጢአተ ኮነ’ ‘እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ ፤ ቦኑ በከንቱ ኪዳንኪ ኮነ’ ‘በምን ምግባሬ ፊትሽን አየዋለሁ’ ‘እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኜያለሁ’ ወዘተ የሚሉት እልፍ ምስጋናዎች ቤተ ክርስቲያን ልጆችዋ በምግባሬ እጸድቃለሁ ብለው ተስፋ እንዳያደርጉና በክርስቶስ በማመናቸው (በሥጋ እንደመጣና ከድንግል ማርያም እንደተወለደ ማመንን ይጨምራል) እና በእግዚአብሔር ጸጋ ወይም ቸርነት እንደሚጸድቁ (እምነት + ሥራ + ጸጋ) ታስተምራለች፡፡

የድንግል ማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም መባሉ የሚያበሳጨው ካለ መጽሐፍ ቅዱስ ‘ነገር ግን በፍቅር እርስ በእርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ’ ይላል፡፡ ገላ. 5፡13 እንኳንስ ለአምላክ እናት አጠገብህ ላለው ወንድምህም በፍቅር ባሪያ ብትሆን ትጠቀማለህ እንጂ አትጎዳም፡፡ ለድንግል ማርያም ባሪያዋና ታዛዥዋ ብትሆን ግን ብዙ ትጠቀማለህ፡፡ ክርስቲያኖች ሆይ ልንገራችሁ ሁሉን ትታችሁ ለድንግል ማርያም ብቻ ታዘዙ፡፡ የእርስዋ ትእዛዝ አንድ ነው ‘የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ’ ዮሐ. 2፡5


+ ተአምራትን እንዴት እናያቸዋለን? +

መጽሐፍ ቅዱስ ‘የሐዋርያት ሥራ’ን የመሰሉ ሰዎች በእግዚአብሔር ኃይል የሠሩትን ሥራ የሚተርኩ መጻሕፍት ያለበት መጽሐፍ ነው፡፡ ‘የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሏቸው’ በማለት ሕያዋን መጽሐፍት ወይም ተንቀሳቃሽ መጽሐፍ ቅዱስ /Living bible or moving bible/ ተብለው የሚጠሩትን የቅዱሳንን ሕይወት እንድናጠና እና በኑሮአቸው እንድንመስላቸው ያሳስበናል፡፡ (ዕብ. 13፡7) ቅዱስ ጳውሎስ ‘እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ’ ብሎ እንደነገረን ክርስቶስን ለመምሰል የጳውሎስን የሕይወት ታሪክ ማጥናት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ (1ቆሮ. 11፡1) ራሱ ጳውሎስም ከእርሱ የቀደሙ የእምነት አርበኞችን አስደናቂ ታሪክ ከዘረዘረ በኋላ ‘ሁሉን እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል’ ብሏል፡፡ (ዕብ. 11፡32) ጳውሎስ የቅዱሳኑን ታሪክ ለመተረክ ያጠረው ጊዜ እንጂ ፍቅር አልነበረም፡፡

እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ ያደረገውን መስማትም የቅዱሳን ታሪክ አካል ነው፡፡ ‘በሐዋርያት እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ’ ‘እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር’ እንደሚል እግዚአብሔር በባሪያዎቹ እጅ ታላላቅ ተአምራት ያደርጋል፡፡ (ሐዋ. 2፡42 ፣ 19፡11) የእስራኤል ንጉሥ ‘ኤልሳዕ ያደረገውን ተአምር እስቲ ንገረኝ’ እያለ ግያዝን እየጠየቀ በደስታ ይሰማ እንደነበረ የእግዚአብሔር ቅዱሳን ያደረጉትን ተአምር መስማት ለምናምን ሰዎች እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው፡፡ (2ነገሥ. 8፡4)


>>Click here to continue<<

እልመስጦአግያ+++




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)