❗️ አስቸኳይ የድረሱልን ጥሪ ❗️
ከዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም
-------------------------------
ምሥራቅ ሐረርጌ ,ኢትዮጵያ
ታኅሣሥ ፩ ፳፻፲ወ፭ ዓ/ም
የበርካታ መናንያን መኖሪያ ታላቁ የዝቋላ ደብረ ከዋክብት ገዳም "በታጠቁ ኃይሎች" እየታመሰ ይገኛል ፡፡ ማምሻው የታጠቁ ኃይሎት በሁሉም አቅጣጫ ወደ ገዳሙ ሰብረው በመግባት መነኮሳትን በማገት ገዳሙን እያመሱት ይገኛል ፡፡ ሚዲያችን የሚመለከታቸውን አካላት ቦታው ድረስ በመደወል እየደረሰባቸው የሚገኘውን እንግልት እንዲህ በማለት ገልጸዋል "ከገዳሙ የጥበቃ ኃይሎች የሚገኙትን መሣሪያዎች በከበባ ነጥቀዋል፣ ገዳሙን በሁሉም አቅጣጫ በመግባት እያስጨነቁ ይገኛሉ ሦስት አገልጋዮችን አግተዋቸዋል ድረሱል ድረሱል" የሚል ድምፅን አሰምተዋል፡፡ የወረዳ ቤተክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በመሆን ለመታደግ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
የሚመለከተው የመንግሥት የጸጥታ መዋቅር በአስቸኳይ የመነኮሳትን እንግልትና የድረሱልን ድምጽ በመስማት አስፈላጊው የፀጥታ ኃይል ወደ ቦታው እንዲልክና ለሀገር የሚጸልዩ መነኮሳትንና ደቀመዛሙርት እንዲታደግ እንጠይቃለን ሲል የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ሚዲያ ገልጿል።
>>Click here to continue<<