TG Telegram Group & Channel
ቅንጭብጭብ | United States America (US)
Create: Update:

አፍሪካን በ 352 ቀናት...

አፍሪካን በ352 ቀን ሮጦ የጨረሰው 🌍

ይህ ሰው ከባድ ፈተናዎችን ሲጋፈጥ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት ከቱርኳ ኢስታንቡል እስከ እንግሊዟ ለንደን ድረስ ሮጧል፡፡ ለአንድ ሳምንት በህይወት ተቀብሯል፡፡ መኪና እየጎተተም ማራቶን ለመሮጥ ሞክሯል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካን ርዝመት መሮጥ የህይወቱ ከባዱ ፈተና ነበር ተብሏል፡፡

ረስ ኩክ ይባላል፡፡ እንግሊዛዊ ነው፡፡ ከ352 ቀናት በፊት በደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው የመጨረሻው ደቡባዊ ጫፍ ላይ ነበር የሚገኘው፡፡ ቦታዋ ደሞ የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ አጉላስ ናት፡፡ ታዲያ ማድረግ አይደለም ለማሰብ የሚከብደውን ተግባር አንድ ብሎ ጀመረ፡፡ በሩጫ አፍሪካን መጨረስ፡፡ በሩጫ ከደቡብ እስከ ሰሜን ጫፍ ማቋረጥ፡፡ መንገዱ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡

ከፍተኛ የሆነ የጤና እክል ገጥሞት ያውቃል፣ መሳርያ ተደግኖበት ተዘርፏል፣ ቪዛ ለማግኘት ተቸግሯል፣ በሰሃራ በረሃ ሙቀት ነዷል፣ የተለያዩ አስፈሪና ከባድ ተራራዎችን እንዲሁም ጥቅጥቅ ደኖችን አቋርጧል፡፡

ለዚህም እንደ አብነት ጉዞውን ከጀመረ በኋላ በ200ኛ ቀኑ ላይ በጤና ችግር ምክንያት ናይጄሪያ ውስጥ በሚገኝ ጤና ተቋም ገብቷል፡፡ ከምርመራው በኋላም በቀን የሚጓዘውን ርቀት መጠን ቀንሶ በማስታገሻዎች ጉዞውን ቀጠለ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ኩክ መነሻውን ከደቡብ አፍሪካ ደቡባዊ ጫፍ / ኬፕ አጉላስ / እስከ ከሰሜን አፍሪካ ሰሜናዊ ጫፍ ቱኒዚያ /ራስ አንጀላ/ ድረስ ሮጠ፡፡ የማይታሰበውን አሳካ፤ ሊደረግ አይችልም ተብሎ የታመነውንም አደረገ፡፡ በዚህም 16 ሀገራትን አቋርጧል፤ 16 ሺሕ ኪሎ ሜትሮችን አካሏል፡፡ ጠቅላላ የሮጠው በማራቶን ቢቀየር ደሞ 376 ማራቶን የመሮጥ ያህል ነው ይለናል የዘጋርዲያን ዘገባ፡፡ የሆነው ሆኖ ኩክ የመጀመሪያው የአፍሪካን አህጉር ርዝመት የሮጠ ሰው ሆኗል፡፡

ኩክ በሩጫው ጊዜያት ከ756 ሺሕ ዶላር በላይ መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ይህንን ገንዘብም በሚያስገርም ሁኔታ ለሁለት የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደሚያውለው ገልጿል፡፡

ኩክ ጉዞውን በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ለጋዜጣው እንደገለጸው ከቤተሰብ ተለይቶ ይህንን ከባድ ጉዞ መጀመር ከባድ እንደነበር ገልጾ በዛ ላይም ህመም ይሰማው እንደነበርና ሌሎች ችግሮችም እንዳጋጠሙት ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ህልሙን ሳያሳካ መቆም እንዳልፈለገ ጠቁሟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ሰዎች ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ለመሆን ጉዞውን እንደጀመረ ጠቅሶ በመጨረሻም እንዳለው ተሳክቶለት የጽናት ምሳሌ ለመሆን ችሏል፡፡

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi

አፍሪካን በ 352 ቀናት...

አፍሪካን በ352 ቀን ሮጦ የጨረሰው 🌍

ይህ ሰው ከባድ ፈተናዎችን ሲጋፈጥ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት ከቱርኳ ኢስታንቡል እስከ እንግሊዟ ለንደን ድረስ ሮጧል፡፡ ለአንድ ሳምንት በህይወት ተቀብሯል፡፡ መኪና እየጎተተም ማራቶን ለመሮጥ ሞክሯል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካን ርዝመት መሮጥ የህይወቱ ከባዱ ፈተና ነበር ተብሏል፡፡

ረስ ኩክ ይባላል፡፡ እንግሊዛዊ ነው፡፡ ከ352 ቀናት በፊት በደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው የመጨረሻው ደቡባዊ ጫፍ ላይ ነበር የሚገኘው፡፡ ቦታዋ ደሞ የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ አጉላስ ናት፡፡ ታዲያ ማድረግ አይደለም ለማሰብ የሚከብደውን ተግባር አንድ ብሎ ጀመረ፡፡ በሩጫ አፍሪካን መጨረስ፡፡ በሩጫ ከደቡብ እስከ ሰሜን ጫፍ ማቋረጥ፡፡ መንገዱ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡

ከፍተኛ የሆነ የጤና እክል ገጥሞት ያውቃል፣ መሳርያ ተደግኖበት ተዘርፏል፣ ቪዛ ለማግኘት ተቸግሯል፣ በሰሃራ በረሃ ሙቀት ነዷል፣ የተለያዩ አስፈሪና ከባድ ተራራዎችን እንዲሁም ጥቅጥቅ ደኖችን አቋርጧል፡፡

ለዚህም እንደ አብነት ጉዞውን ከጀመረ በኋላ በ200ኛ ቀኑ ላይ በጤና ችግር ምክንያት ናይጄሪያ ውስጥ በሚገኝ ጤና ተቋም ገብቷል፡፡ ከምርመራው በኋላም በቀን የሚጓዘውን ርቀት መጠን ቀንሶ በማስታገሻዎች ጉዞውን ቀጠለ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ኩክ መነሻውን ከደቡብ አፍሪካ ደቡባዊ ጫፍ / ኬፕ አጉላስ / እስከ ከሰሜን አፍሪካ ሰሜናዊ ጫፍ ቱኒዚያ /ራስ አንጀላ/ ድረስ ሮጠ፡፡ የማይታሰበውን አሳካ፤ ሊደረግ አይችልም ተብሎ የታመነውንም አደረገ፡፡ በዚህም 16 ሀገራትን አቋርጧል፤ 16 ሺሕ ኪሎ ሜትሮችን አካሏል፡፡ ጠቅላላ የሮጠው በማራቶን ቢቀየር ደሞ 376 ማራቶን የመሮጥ ያህል ነው ይለናል የዘጋርዲያን ዘገባ፡፡ የሆነው ሆኖ ኩክ የመጀመሪያው የአፍሪካን አህጉር ርዝመት የሮጠ ሰው ሆኗል፡፡

ኩክ በሩጫው ጊዜያት ከ756 ሺሕ ዶላር በላይ መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ይህንን ገንዘብም በሚያስገርም ሁኔታ ለሁለት የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደሚያውለው ገልጿል፡፡

ኩክ ጉዞውን በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ለጋዜጣው እንደገለጸው ከቤተሰብ ተለይቶ ይህንን ከባድ ጉዞ መጀመር ከባድ እንደነበር ገልጾ በዛ ላይም ህመም ይሰማው እንደነበርና ሌሎች ችግሮችም እንዳጋጠሙት ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ህልሙን ሳያሳካ መቆም እንዳልፈለገ ጠቁሟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ሰዎች ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ለመሆን ጉዞውን እንደጀመረ ጠቅሶ በመጨረሻም እንዳለው ተሳክቶለት የጽናት ምሳሌ ለመሆን ችሏል፡፡

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi


>>Click here to continue<<

ቅንጭብጭብ






Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)