TG Telegram Group & Channel
ቅንጭብጭብ | United States America (US)
Create: Update:

ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

....

ነገን ፍለጋ
ተስፋአብ ተሾመ

ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

....

ነገን ፍለጋ
ተስፋአብ ተሾመ


>>Click here to continue<<

ቅንጭብጭብ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)