TG Telegram Group & Channel
✞✞✞ በእንተ ቅዱሳን ✞✞✞ | United States America (US)
Create: Update:

📖 አቡነ_ኪሮስ 📖
አቡነ ኪሮስ አባታቸው ንጉስ ዮናስ እናታቸው አንስራ ይባላሉ፡፡ ሀገራቸው ሮም ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ወለዱ፡፡
💎አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡ በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስተው ወስዶው ገነትን አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰቷቸዋል።

💎ቃል ኪዳናቸውም ፡- መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹህ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በሕግ በሥጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው በዛሬዋ ዕለት #ሐምሌ 8 ዐረፈዋል
ከቅዱሳን ሁሉ ረድኤታቸውንና በረከታቸውን አሳድርብን፡፡

በድፍረት፣ በትዕቢት በመናቅም በቅዱሳን ላይ የሚናገሩ የሽንገላ አንደበት ዲዳ ይሁኑ መዝሙር 30፡18 አንዳንዶችን በቅዱሳን ላይ ተነስቷልና ይቅር ይበላቸው፤ ልቦና ይስጣቸው መድኃኔዓለም የሚያደርጉትን አያቁምና ይቅር በላቸው ያለው ጌታ ይቅር ይበላቸው፡፡ …እንግዲህ እግዚአብሔር የመረጠውን ማን ይከሳል።
💎ሮሜ 8፡28-31 “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል እናንተን የጣለ እኔን ይጥላል እኔን የጣለ የላከኝን ይጥላል።” ሉቃ. 10፡16

💎“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ መዝሙር” 111፡6

💎…ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል… እውነት እላችዃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም…+++። ማቴ.10፡40-42

📖 አቡነ_ኪሮስ 📖
አቡነ ኪሮስ አባታቸው ንጉስ ዮናስ እናታቸው አንስራ ይባላሉ፡፡ ሀገራቸው ሮም ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ወለዱ፡፡
💎አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡ በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስተው ወስዶው ገነትን አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰቷቸዋል።

💎ቃል ኪዳናቸውም ፡- መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹህ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በሕግ በሥጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው በዛሬዋ ዕለት #ሐምሌ 8 ዐረፈዋል
ከቅዱሳን ሁሉ ረድኤታቸውንና በረከታቸውን አሳድርብን፡፡

በድፍረት፣ በትዕቢት በመናቅም በቅዱሳን ላይ የሚናገሩ የሽንገላ አንደበት ዲዳ ይሁኑ መዝሙር 30፡18 አንዳንዶችን በቅዱሳን ላይ ተነስቷልና ይቅር ይበላቸው፤ ልቦና ይስጣቸው መድኃኔዓለም የሚያደርጉትን አያቁምና ይቅር በላቸው ያለው ጌታ ይቅር ይበላቸው፡፡ …እንግዲህ እግዚአብሔር የመረጠውን ማን ይከሳል።
💎ሮሜ 8፡28-31 “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል እናንተን የጣለ እኔን ይጥላል እኔን የጣለ የላከኝን ይጥላል።” ሉቃ. 10፡16

💎“ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ መዝሙር” 111፡6

💎…ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል… እውነት እላችዃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም…+++። ማቴ.10፡40-42


>>Click here to continue<<

✞✞✞ በእንተ ቅዱሳን ✞✞✞




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)