የኡዱሕያ መስፈርቶች
1ኛ, ከቤት እንስሳት መሆን አለበት።
እነርሱም ፡- ግመል ከብት በግ እና ፍየል
2ኛ, በሸሪዓ ለተገደበው እድሜ መድረስ አለበት።
ግመል ከኾነ 5 ዓመት
ከብት ከኾነ 2 ዓመት
ፍየል ከኾነ 1 ዓመት
በግ ከኾነ 6 ወር የሞላው
3ኛ, ከነውር (ከዓይብ) የጠራ መሆን አለበት።
አንድ ሰው ኡዱሕያ ማረድ ከፈለግ በሚያርደው እንስሳ ላይ የተጠቀሱት ነገሮች መሟላት አለባቸው።
🛖ቅርጫ ማድረግ የፈለገ ሰው
በግ ወይም ፍየል ከኾነ ለ1 ሰው ብቻ
በሬ ወይም ግመል ከኾነ ለ7 ሰው መካፈል ይቻላል
👉 እንስሳቶችን ስናርድ ደግሞ አስተራረዳችንን ማሳመር አለብን። እነሱም ነፍስ አላቸው አይናገሩም ብሎ እነሱን ማሰቃየት ተገቢ አይደለም።
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إِنَّ اللَّهَ كَتَبَ الْإِحْسَانَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ، فَإِذَا قَتَلْتُمْ فَأَحْسِنُوا الْقِتْلَةَ، وَإِذَا ذَبَحْتُمْ فَأَحْسِنُوا الذَّبْحَ، وَلْيُحِدَّ أَحَدُكُمْ شَفْرَتَهُ فَلْيُرِحْ ذَبِيحَتَهُ﴾
👉አላህ ኢኽሳንን (ማሳመርን) በሁሉም ነገሮች ላይ ፅፏል። የገደላችሁ እንደሆነ አገዳደልን አሳምሩ። አንዳችሁ ባረደ ግዜ አስተራረዱን ያሳምር ማረጃውን ይሳል። የሚታረደውንም እንስሳም ያሳርፍ። 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1955
@heppymuslim29
>>Click here to continue<<