TG Telegram Group & Channel
ሃይማኖት አንድ ናት | United States America (US)
Create: Update:

ኒቆዲሞስ

ኒቆዲሞስ ማለት የሕዝብ ድል (የሕዝብ አለቃ ) ማለት ሲሆን ስሙ በዮሐንስ ወንጌል ብቻ ተጽፏል። የሳን ሕድሪን (የአይሁድ ሸንጎ ) አባል ሲሆን  ምሁረ ኦሪት ነበር። ከጌታም በቀጥታ የተማረ ነው። ጥያቄ ጠይቆ የተመለሰለት፡ ከገማልያል ንባብ ከጌታ ምስጢር ያደላደለ።

አንዳንድ ምሑራን ኒቆዲሞስን ተከራርካሪ ነው የሚሉት አሉ ነገር ግን ተከራካሪ ብቻ ሳይሆን ጠያቂም ነው። እንደ ዘካርያስ ሳይጠራጠር ያመነ ነው፡፡ መምህርነቱን ለማጽናት መጣ ግን አላዋቂነቱ ተነገረው። በአይሁድ ዘንድ የተከበረ የተማረ ባለጠጋም ነበር። ወደ ጌታ መጣ ካልታወቀ መምህር ዘንድ ለመማር ቀረበ። ጌታን እንደ ታዋቂ መምህር ስለማያዩት “ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦”

ኒቆዲሞስ እውነትን ለማወቅ የሚጓጓ ነበር። በሌሊት መጣ። በሌሊት የመጣበትን ምክንያት አንዱ ፍርሃት ሲሆን ፦ ያልተማረ እንዳይባል ነቀፋ ፈርቶ ነው፡፡ ኒቆዲሞሰ መምህር ይሁን እንጂ ከፍርሃት ነጻ አልነበረም፡፡ ከርሱ ጋር የታየውን ሰው ከምኩራብ ይለዩት ነበር፡፡ “ወላጆቹ አይሁድን ስለ ፈሩ ይህን አሉ፤ እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኵራብ እንዲያወጡት አይሁድ ከዚህ በፊት ተስማምተው ነበርና” ዮሐ.9:25

ሌላው ምክንያት መምህርነቱ ካልተመሰከረለት መምህር መገኘቱ ሲሆን ሶስተኛው ምክንያት ደግሞ  ቀን ለውይይት አይመችም ሕዝብ ጣልቃ እንዳይገባ ብሎ ነው ይላሉ መተርጉማነ ወንጌል፡፡ ኒቆዲሞስ ጌታን የቆጠረው እንደ አንድ ጻድቅ  ነበር እንጂ መሲህ አልመሰለውም  “በሕዝብም መካከል ስለ እርሱ ብዙ ማንጐራጐር ነበረ፤ አንዳንዱም፦ ደግ ሰው ነው፤ ሌሎች ግን፦ አይደለም፥ ሕዝቡን ግን ያስታል ይሉ ነበር።” ዮሐ.7:12

ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ኒቆዲሞስ ሲናገር “ጌታ ኒቆዲሞስን በነቀፋ አልተቀበለውም አላሳፈረውም አልገሰጸውም ይልቁንም ትልቁን እና ጥልቁን ነገረ ሃይማኖትን አናገረው እንጂ” ይላል፡፡ ኒቆዲሞስ ስለ ጌታ የተወሰነ እውቀት ቢኖረውም ገና ያልጠራ ሰብአዊ ሐሳብ ነበረው። ተአምራቱን ስላየ እንደ ነቢይ አይቶታል። ጌታ ታዲያ ለምን በቀን አልመጣህም አላለውም  “አይጮኽም ቃሉንም አያነሣም፥ ድምፁንም በሜዳ አያሰማም የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስንም ክር አያጠፋም፤ በእውነት ፍርድን ያወጣል።” እንዲል ኢሳ.42፡2 “አይከራከርም አይጮህምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም”ማቴ 12፡19   ዮሐ. 12፡47

የኒቆዲሞስ የንግግር መነሻ

“መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው።”ኒቆዲሞስ ያላወቀው ነገር ቢኖር ተአምር ያደረገ ሁሉ ከእግዚአብሔር አለመሆኑን ነው። ዮሐንስ አፈወርቅ ሲተረጉመው፦ “ጌታ የመጣው ተአምራት ሊያደርግ ሳይሆን ነቢያትን እና ሕግን ለመፈጸም ነው” ይላል  “እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም” ማቴ.5፡17

 ጌታችን ለኒቆዲሞስ ሲናገር መምህር ብቻ መሆኑ ቀርቶ ከሁሉ አስቀድሞ መድኃኔ ዓለም እንደሆነ አረጋገጠለት፡፡ ከክርስቶስ ጋር ለመሆን አስፈላጊው ነገር ተገቢ መሆን ሳይሆን ዳግም መወለድ አስፈላጊ መሆኑን ማወቅ እንዳለበት ነገረው፡፡

ጌታችን ለኒቆዲሞስ “ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው” ዮሐ.3፡3 
ኒቆዲሞስ የሚያስፈልገው ነገር እንደገና መወለድ ስለነበር  ጌታ “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ” አለው። በዚህ ንግግር ውስጥ መንፈሳዊ ህይወት ከሥጋዊ ሕይወት ወይም ከአእምሮ እውቀት በላይ መሆኑን የሚያሳይ መልእክትን ይዟል።

 ይኽንን መልስ ኒቆዲሞስ መሸከም የሚችለው አልነበረም፡፡ “እንደገና መወለድ ሲል ሌላ መወለድ፤ ሌላ እውቀት ከምድር ከተፈጥሮ አስተሳሰብ በላይ የላቀ እንዳለ ነገረው ” “ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው” ቁ.4

ሰው እንዴት ዳግመኛ ሊወለድ ይችላል አለው፡፡ ኒቆዲሞስ ምስጢሩ የረቀቀበት የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ባለማወቁ ነው፡፡ የመወለዱን ምስጢር ሳይሆን መንገዱን ጠየቀ እንዴት? ይህ ሳራን ያስታውሰናል ትወልጃለሽ ስትባል ሳቀች በጣም ስላረጀች የሚሆን አልመሰላትም፡፡ ሁለተኛ ወደ ማሕጸን እንዴት ሊገባ ይችላል? አለ፡፡ ይኽ መንፈሳዊ ነገሮችን እንዴት ወደራሳችን ሀሳብ እንደምንጎትት ያሳያል።

ሌላው ኒቆዲሞስ በወቅቱ የመናፍቃንን ጥያቄን ይዞ ነበር የመጣው። ለጥያቄውም መልስ አላገኘም ነበር። “አይወለድም፣ እንዴት ሥጋ ሊለብስ ይችላል” የሚል ክርክር በአካባቢው  ነበር። ስለሆነም በራሳቸው መረዳት ተጉዘው ይስቱ ነበር። ኒቆዲሞስ መልሱ አልገባው ቢል ጥያቄውን ወደ ታች ወሰደው፡፡ “ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም” 1ቆሮ.2፡14

ኒቆዲሞስ መምህር ነው ነገር ግን ሁለት ነገር ከበደው
  ፩.ዳግም ስለ መወለድ ፦ ለመምህር በሚያምነው መሠረታዊ ነገር ላይ እውቀት ማጣት ትልቅ ውድቀት ነው። ዛሬም ይኽው ነው። መምህራን ነን ብለው ከመሰረታዊ ትምህርት የሚጎድሉ በርካታ ናቸው፡፡ በየጠበል ሰፈር የአጋንንት ልፍለፋ ብቻ ሰምተው ራሳቸውን መምህራን ያደረጉም ያየንበት ዘመን ነው፡፡ ዘይት በመቀባት የሚነግዱም በመምህር" ስም ነጋዴዎች ናቸው። ሃይማኖትን ከድንቁርና አስተሳሰብ ማላቀቅና በቲዎሎጂ መምራት ይገባል፡፡ 

    ፪. “የእግዚአብሔር መንግሥት” ኒቆዲሞስ ይኽንን  ቃል  በአይሁድ ትምህርት ሰምቶ አያውቅም፡፡ በብሉይ ትምህርት ውስጥም የለም፡፡ የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚመሠርተው እርሱ ነው። እነርሱ የሮማን መንግሥት መወደቅ ነው የሚጠብቁት፡፡ “ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም” ኒቆዲሞስ የጥያቄው መልስ አስገረመው፡፡

ኒቆዲሞስ “አይችልም” ሲል ጌታ “ይቻላል” አለ። የመሬቱን እና የሰማዩን ልደት የሚለየው “መንፈስ” ነው።  ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፡፡ ጌታ ሰው ዳግመኛ መወለድ እንዳለበት አስተማረው ።

የቀደመው ፍጥረት ውሐ፣ አፈር፣ ነፋስ ነው። የአሁኑ ፍጥረት ከውኃና ከመንፈስ ነው፡፡ ሰው እንዴት ከውኃ ይወለዳል ለሚለው ጥያቄ “ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው” የእኔ ጥያቄ “ሰው እንዴት ከአፈር ይፈጠራል” የሚል ይሆናል። ያ አፈር አጥንት፣ ቆዳ፣ ክፈለ አካል ሆኗል ቀለሙ ይለያያል፡፡

 ከውኃ መወለድ የሚታየው በእምነት ነው “ውኃው የሚለወጠው በእምነት ነው” “እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ" ሲል ዘፍ.2፤7 

“ሕይወትን በሚሰጥ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን” ጸሎተ ሃይማኖት “ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም” ይላል።

ኒቆዲሞስ

ኒቆዲሞስ ማለት የሕዝብ ድል (የሕዝብ አለቃ ) ማለት ሲሆን ስሙ በዮሐንስ ወንጌል ብቻ ተጽፏል። የሳን ሕድሪን (የአይሁድ ሸንጎ ) አባል ሲሆን  ምሁረ ኦሪት ነበር። ከጌታም በቀጥታ የተማረ ነው። ጥያቄ ጠይቆ የተመለሰለት፡ ከገማልያል ንባብ ከጌታ ምስጢር ያደላደለ።

አንዳንድ ምሑራን ኒቆዲሞስን ተከራርካሪ ነው የሚሉት አሉ ነገር ግን ተከራካሪ ብቻ ሳይሆን ጠያቂም ነው። እንደ ዘካርያስ ሳይጠራጠር ያመነ ነው፡፡ መምህርነቱን ለማጽናት መጣ ግን አላዋቂነቱ ተነገረው። በአይሁድ ዘንድ የተከበረ የተማረ ባለጠጋም ነበር። ወደ ጌታ መጣ ካልታወቀ መምህር ዘንድ ለመማር ቀረበ። ጌታን እንደ ታዋቂ መምህር ስለማያዩት “ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦”

ኒቆዲሞስ እውነትን ለማወቅ የሚጓጓ ነበር። በሌሊት መጣ። በሌሊት የመጣበትን ምክንያት አንዱ ፍርሃት ሲሆን ፦ ያልተማረ እንዳይባል ነቀፋ ፈርቶ ነው፡፡ ኒቆዲሞሰ መምህር ይሁን እንጂ ከፍርሃት ነጻ አልነበረም፡፡ ከርሱ ጋር የታየውን ሰው ከምኩራብ ይለዩት ነበር፡፡ “ወላጆቹ አይሁድን ስለ ፈሩ ይህን አሉ፤ እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኵራብ እንዲያወጡት አይሁድ ከዚህ በፊት ተስማምተው ነበርና” ዮሐ.9:25

ሌላው ምክንያት መምህርነቱ ካልተመሰከረለት መምህር መገኘቱ ሲሆን ሶስተኛው ምክንያት ደግሞ  ቀን ለውይይት አይመችም ሕዝብ ጣልቃ እንዳይገባ ብሎ ነው ይላሉ መተርጉማነ ወንጌል፡፡ ኒቆዲሞስ ጌታን የቆጠረው እንደ አንድ ጻድቅ  ነበር እንጂ መሲህ አልመሰለውም  “በሕዝብም መካከል ስለ እርሱ ብዙ ማንጐራጐር ነበረ፤ አንዳንዱም፦ ደግ ሰው ነው፤ ሌሎች ግን፦ አይደለም፥ ሕዝቡን ግን ያስታል ይሉ ነበር።” ዮሐ.7:12

ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ኒቆዲሞስ ሲናገር “ጌታ ኒቆዲሞስን በነቀፋ አልተቀበለውም አላሳፈረውም አልገሰጸውም ይልቁንም ትልቁን እና ጥልቁን ነገረ ሃይማኖትን አናገረው እንጂ” ይላል፡፡ ኒቆዲሞስ ስለ ጌታ የተወሰነ እውቀት ቢኖረውም ገና ያልጠራ ሰብአዊ ሐሳብ ነበረው። ተአምራቱን ስላየ እንደ ነቢይ አይቶታል። ጌታ ታዲያ ለምን በቀን አልመጣህም አላለውም  “አይጮኽም ቃሉንም አያነሣም፥ ድምፁንም በሜዳ አያሰማም የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስንም ክር አያጠፋም፤ በእውነት ፍርድን ያወጣል።” እንዲል ኢሳ.42፡2 “አይከራከርም አይጮህምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም”ማቴ 12፡19   ዮሐ. 12፡47

የኒቆዲሞስ የንግግር መነሻ

“መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው።”ኒቆዲሞስ ያላወቀው ነገር ቢኖር ተአምር ያደረገ ሁሉ ከእግዚአብሔር አለመሆኑን ነው። ዮሐንስ አፈወርቅ ሲተረጉመው፦ “ጌታ የመጣው ተአምራት ሊያደርግ ሳይሆን ነቢያትን እና ሕግን ለመፈጸም ነው” ይላል  “እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም” ማቴ.5፡17

 ጌታችን ለኒቆዲሞስ ሲናገር መምህር ብቻ መሆኑ ቀርቶ ከሁሉ አስቀድሞ መድኃኔ ዓለም እንደሆነ አረጋገጠለት፡፡ ከክርስቶስ ጋር ለመሆን አስፈላጊው ነገር ተገቢ መሆን ሳይሆን ዳግም መወለድ አስፈላጊ መሆኑን ማወቅ እንዳለበት ነገረው፡፡

ጌታችን ለኒቆዲሞስ “ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው” ዮሐ.3፡3 
ኒቆዲሞስ የሚያስፈልገው ነገር እንደገና መወለድ ስለነበር  ጌታ “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ” አለው። በዚህ ንግግር ውስጥ መንፈሳዊ ህይወት ከሥጋዊ ሕይወት ወይም ከአእምሮ እውቀት በላይ መሆኑን የሚያሳይ መልእክትን ይዟል።

 ይኽንን መልስ ኒቆዲሞስ መሸከም የሚችለው አልነበረም፡፡ “እንደገና መወለድ ሲል ሌላ መወለድ፤ ሌላ እውቀት ከምድር ከተፈጥሮ አስተሳሰብ በላይ የላቀ እንዳለ ነገረው ” “ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው” ቁ.4

ሰው እንዴት ዳግመኛ ሊወለድ ይችላል አለው፡፡ ኒቆዲሞስ ምስጢሩ የረቀቀበት የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ባለማወቁ ነው፡፡ የመወለዱን ምስጢር ሳይሆን መንገዱን ጠየቀ እንዴት? ይህ ሳራን ያስታውሰናል ትወልጃለሽ ስትባል ሳቀች በጣም ስላረጀች የሚሆን አልመሰላትም፡፡ ሁለተኛ ወደ ማሕጸን እንዴት ሊገባ ይችላል? አለ፡፡ ይኽ መንፈሳዊ ነገሮችን እንዴት ወደራሳችን ሀሳብ እንደምንጎትት ያሳያል።

ሌላው ኒቆዲሞስ በወቅቱ የመናፍቃንን ጥያቄን ይዞ ነበር የመጣው። ለጥያቄውም መልስ አላገኘም ነበር። “አይወለድም፣ እንዴት ሥጋ ሊለብስ ይችላል” የሚል ክርክር በአካባቢው  ነበር። ስለሆነም በራሳቸው መረዳት ተጉዘው ይስቱ ነበር። ኒቆዲሞስ መልሱ አልገባው ቢል ጥያቄውን ወደ ታች ወሰደው፡፡ “ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም” 1ቆሮ.2፡14

ኒቆዲሞስ መምህር ነው ነገር ግን ሁለት ነገር ከበደው
  ፩.ዳግም ስለ መወለድ ፦ ለመምህር በሚያምነው መሠረታዊ ነገር ላይ እውቀት ማጣት ትልቅ ውድቀት ነው። ዛሬም ይኽው ነው። መምህራን ነን ብለው ከመሰረታዊ ትምህርት የሚጎድሉ በርካታ ናቸው፡፡ በየጠበል ሰፈር የአጋንንት ልፍለፋ ብቻ ሰምተው ራሳቸውን መምህራን ያደረጉም ያየንበት ዘመን ነው፡፡ ዘይት በመቀባት የሚነግዱም በመምህር" ስም ነጋዴዎች ናቸው። ሃይማኖትን ከድንቁርና አስተሳሰብ ማላቀቅና በቲዎሎጂ መምራት ይገባል፡፡ 

    ፪. “የእግዚአብሔር መንግሥት” ኒቆዲሞስ ይኽንን  ቃል  በአይሁድ ትምህርት ሰምቶ አያውቅም፡፡ በብሉይ ትምህርት ውስጥም የለም፡፡ የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚመሠርተው እርሱ ነው። እነርሱ የሮማን መንግሥት መወደቅ ነው የሚጠብቁት፡፡ “ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም” ኒቆዲሞስ የጥያቄው መልስ አስገረመው፡፡

ኒቆዲሞስ “አይችልም” ሲል ጌታ “ይቻላል” አለ። የመሬቱን እና የሰማዩን ልደት የሚለየው “መንፈስ” ነው።  ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፡፡ ጌታ ሰው ዳግመኛ መወለድ እንዳለበት አስተማረው ።

የቀደመው ፍጥረት ውሐ፣ አፈር፣ ነፋስ ነው። የአሁኑ ፍጥረት ከውኃና ከመንፈስ ነው፡፡ ሰው እንዴት ከውኃ ይወለዳል ለሚለው ጥያቄ “ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው” የእኔ ጥያቄ “ሰው እንዴት ከአፈር ይፈጠራል” የሚል ይሆናል። ያ አፈር አጥንት፣ ቆዳ፣ ክፈለ አካል ሆኗል ቀለሙ ይለያያል፡፡

 ከውኃ መወለድ የሚታየው በእምነት ነው “ውኃው የሚለወጠው በእምነት ነው” “እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ" ሲል ዘፍ.2፤7 

“ሕይወትን በሚሰጥ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን” ጸሎተ ሃይማኖት “ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም” ይላል።


>>Click here to continue<<

ሃይማኖት አንድ ናት




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)