TG Telegram Group & Channel
ከራድዮን | United States America (US)
Create: Update:

#ጭንቀት - አባታዊ ምክር

እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን ሲተረጉመው "ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ይለዋል" የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም፣ ውጥረት ወይም ሕመም ማለት ነው። ጭንቀት ለሕይወታችን ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው። ስለሆነም የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው? ስንል ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን። በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን፣ ከሚቀርቡን፣ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ የምንጠብቀው አለ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶችሊመጣ ይችላል። ✞ስለ ሰወች ያለን ተስፈኝነት አለ። ሌላው ✞ሰዎች ስለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው።

በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን ይችላል። ወይም እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን አድርገን ልንወስድ እንችላለን። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን ይችላል።

ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው።
የቁስ እቃ ፍላጎት እንድንጨነቅ ያደርጋል። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ አሉታዊ መልስ እንሰጣለን። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም ሳይሆን ይቀራል።

ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴ ቤተ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው። ቁሣዊ ሆነን አልተፈጠርንም። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው። መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው። ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው። ግፊቱም፣ ጭንቀቱም፣ ሕመሙና፣ ውጥረቱ፣ በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል። ከእግዚአብሔር ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም። ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም አደርጋለሁ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል።

ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ። እንደገናም ለባርነት ሸጡት። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት በሐሰት ከሰሰችው። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ። በእስር ቤት እያለ ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና ውስጥ ያመጣዋል። ሆኖም ግን ዮሴፍ እንዴት ለመፍታት ሞከረ? ችግሩን እንዴት ተቋቋመው? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ራሱ ዮሴፍ ነበረ። አልተለወጠም። በሁሉም ሁኔታዎች ተመሣሣይ ማንነት፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ነበረው። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ። እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ።

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
____________
@gitim_menfesawi

#ጭንቀት - አባታዊ ምክር

እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን ሲተረጉመው "ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ይለዋል" የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም፣ ውጥረት ወይም ሕመም ማለት ነው። ጭንቀት ለሕይወታችን ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው። ስለሆነም የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው? ስንል ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን። በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን፣ ከሚቀርቡን፣ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ የምንጠብቀው አለ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶችሊመጣ ይችላል። ✞ስለ ሰወች ያለን ተስፈኝነት አለ። ሌላው ✞ሰዎች ስለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው።

በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን ይችላል። ወይም እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን አድርገን ልንወስድ እንችላለን። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን ይችላል።

ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው።
የቁስ እቃ ፍላጎት እንድንጨነቅ ያደርጋል። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ አሉታዊ መልስ እንሰጣለን። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም ሳይሆን ይቀራል።

ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴ ቤተ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው። ቁሣዊ ሆነን አልተፈጠርንም። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው። መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው። ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው። ግፊቱም፣ ጭንቀቱም፣ ሕመሙና፣ ውጥረቱ፣ በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል። ከእግዚአብሔር ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም። ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም አደርጋለሁ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል።

ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ። እንደገናም ለባርነት ሸጡት። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት በሐሰት ከሰሰችው። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ። በእስር ቤት እያለ ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና ውስጥ ያመጣዋል። ሆኖም ግን ዮሴፍ እንዴት ለመፍታት ሞከረ? ችግሩን እንዴት ተቋቋመው? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ራሱ ዮሴፍ ነበረ። አልተለወጠም። በሁሉም ሁኔታዎች ተመሣሣይ ማንነት፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ነበረው። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ። እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ።

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
____________
@gitim_menfesawi


>>Click here to continue<<

ከራድዮን




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)