አንቺ ሴት
እንግዲህ ዘመነ አስተርዕዮም አይደል።
አስተርዕዮም መገለጥ ሲኾን በጽርዕ ቃል ኤፒፋንያ ይባላል። ይህንን የተዋሰው እንግልጣር ኤፒፋኒ (Epiphany)ይላል።
ከተገለጡ ምስጢራት አንዱ የወላዲተ አምላክ ክብርና አማላጅነት መኾኑ ይታወቃል።ከተርኈ ሰማይ ከምስጢረ ሥላሴ እና ከክርስቶስ የባሕርይ ልጅነት ቀጥሎ የሚነገረው ይህ ነው።
የወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት በገሃድ እንደተነገረው የድንግል ማርያምም የእግዚአብሔር እናትነት በገሃድ የተገነረበት ነውና።
አብ ይህ ልጄ ነው እንዳለ እግዚአ ኩሉ ክርስቶስ እናቱን አንቺ ሴት አላት። አብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእም ባሕርይ የምወልድህ ሳለው ልጄ አለው። ጌታም ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ ሲላት ሴት ብሎ እናቱን ጠራት። ሴት እንዲህ ይተረጎማልና።ዘፍ ፪÷፳፫
ቀዳማዊ አዳም እናታችን ሔዋንን ሴት እንዳላት ዳግማዊው አዳም ክርስቶስ (፩ቆሮ ፲፭÷፵፭) እናቱን ሴት አላት ። ዘር ያልቀደመው ልደት ያለ እናት ከአባቱ እንደተወለደ ዘር ያልቀደመው ልደት ያለ አባት ከድንግል ማርያም መወለዱን ያገናዝባል።
ምስጋናውን ይቀበልልን🙏
-------------------------------
@gitim_menfesawi
>>Click here to continue<<