"ለዘተወልደ እምድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ አርዌ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራድዮን ዖፍ ጸዐዳ ንጉሠ ይሁዳ እምዘርዐ ዳዊት ዘመጽአ።"
ድጓ
✨ከራድዮን የሚባል ፀዐዳ ዖፍ አለ ይኸውም ከቤተ መንግስት ወስደው ያኖሩታል። ሰው ሲታመም ወስደው ያቀርቡታል። ያ ሰው የሚሞት የሆነ እንደሆነ አያየውም ፊቱን ይመልስበታል የሚድን የሆነ እንደሆነ ግን ያየዋል ቀርቦም አፉን ከፍ አድርጐ እስትንፋሱን ይቀበለዋል። በእስትንፋሱ ምክንያት ደዌ ከሰውየው ወደሱ ይመለሳል። ታማሚው ይድናል ወፉ ይታመማል፣ነጭ የነበረው ይጠቁራል፣ብርድ ብርድ ይለዋል፣ዋዕይ ሙቀት ሲሻ ወደ አየር ይወጣል። ዋዕይ ሙቀቱ ሲሰማው ሲያይልበት ከባሕር ይገባል። ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በባሕር ኑሮ የቀደመ ጠጉሩን መልጦ አድሶ ይወጣል።
______________________
ከራድዮን የጌታ ምሳሌ
የታመመው ሰው የአዳም ምሳሌ
______________________
እንግዲህ ምን እንላለን ሥላሴ አስቀድመው የአዳምን መበደል ሞትም እንዲመጣበት ያውቃሉና ገና ዓለም ሲፈጠር እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ ለመስጠት ዝግጁ እንደ ነበር የ ከራዲዮን ወፍ አፈጣጠር ምስክር ሆነን ።
✞እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዐል በሰላም አደረሰን✞
________
@gitim_menfesawi
>>Click here to continue<<