+ አባቶቻችን እንዲህ አሉ +
"እሳትና ውኃን ማዋሐድ እንደ ማይቻል በሰው ኃጥያት መፍረድም በራስ ኃጥያት ከመፀፀት ጋር አብሮ አይሄድም"ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው
"የማያማትብ እጅ ቀኙም ግራውም አንድ ነው"አባ ፓስዮስ ዘደብረ አቶስ
"እግዚአብሔር ለኃጥያተኛ ሰው ያለው ፍቅር ፃድቅ ሰው ለእግዚአብሔር ካለው ፍቅር ይበልጣል"አባ አርሳኒ
"ዕለትን የሰጠህ እርሱ ለዕለት የሚበቃህንም ይሰጥሀል"ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
"ለኃጥያተኛ ክንፍህን ዘርጋለት።ኃጥያቱን ልትሸከምለት ባትችል እንኳን ሸፍንለት"ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ
"ይቅር ካላልክ ገነትም ይቅርብህ"አባ ኤፍሬም አረጋዊ
"እጅግ ምርጡ ፀሎት "ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ የፈቀድከውን አድርግልኝ" ማለት ነው"ባህታዊ ቴዎፋን
"እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ÷ምሕረትን÷ርኅራሔን÷ቸርነትን
ትሕትናን÷የዋሕነትን÷ትዕግስትን ልበሱ" ቆላስይስ[፫÷፲፪]
___
@gitim_menfesawi
>>Click here to continue<<