✧የአብስራ ሳሙኤል ✧
ውበት ኪነ-ጥበብ ናት
ከታደሏት ያጌጡባታል
ካልታደሏት ይመኟታል‧‧‧
ያደንቋታል
የአፍንጫ አወራረድ ቤት ይመታል
የጉንጮቿ ስርጉድ ቤት ይደፉል
✧・゚゚:* ──── * ✧・゚:*
ውብ እግዜር የጻፋት ግጥም ትመስላለች
ልብ ብሎ ላያት ሁሉ እንደ ግሉ ትፈታለች
አሁን ለምሳሌ እሷን ያዪ ሴቶች
ቻፒስቲካቸውን አንስተው
የ'ሷን አይነት ቀለም ይቀባሉ
✦•≪───── ⋆⋅☽⋅⋆ ─────≫•✦
ውበት ተዋረሰ ማለት ይሄ አደለ ቅሉ
ልቡ የከጀላት ጎልማሳ ደሞ
"ሚስትማ እንደ እሷ አይነት ነበር እንጂ"
ብሎ ሚስቱን ይገፉል
ውበት አይኑን ሲያውረው
ከማማር ዝሙት ያተርፋል
እሷ ብቻ ናት ማማሯን የማታውቀው
✧・゚: ゚:* ──── * ✧・゚:*
እንደ ግጥም ለራስ ተነባ
አትረካም ታዳሚ ትሻለች
አጀብ አጀብ ባይ አሞጋሽ ትፈልጋለች
ከስንኝ አኳላቶቿ
ግጥም እያዋቀረ የሚያወድሳት
ከሆነችበት ወዳ'ልሆነችበት
በምዕናብ የሚያደርሳት
✧・゚・゚:* ──── *✧・゚✧・゚:*
ምነው እንደጨረቃ
ባማርኩ ብሎ እንደትመኝ የሚያረጋት
ከመሆንና አለመሆን
በምኞት ወላፈን የሚያዋጋት
✦•≪───── ⋆⋅☾⋅⋆ ─────≫•✦
ታዲያ ይሄን ያዩ ቺኮች
አሁንም ገጻቸውን እንደ ጨረቃ ይቀባሉ
ስንቱን ተኩኖ ይቻላል
ስንቱን ይሆናሉ
ወደ ተንጠራራንበት ሁሉ
ፈጣሪ �|አይጠፋም
ቆርጦ የሚቀጥል ቀዶ
የሚሰፋ! አያለፋም ?
✧・゚: * ──── * ✧・゚:*
ታዲያ ውበት ማለት ምን ማለት ይሆን
ያላለቀ ግጥም
ያላለቀ ድርሰት
✾ መድረስ የሚችሉት ነው
ወይስ የቆሙበት
✧・゚: * ──── * ✧・゚:*
ሁሉም በሷ ከተለካ
እሷን ለመምሰል
ገጹን ሸራ ቢያደርገው
ምንድነው ክፋቱ
**ልኬቱ ሳይሆን
መለኪያው ነው ጥፋቱ**
✦•≪─── ⋆⋅☆⋅⋆ ───≫•✦
ቤት የማይመታ መልክ አለ ?
ቤት የማይደፋ ቁመና አለ ?
ገጣሚው ተሳሳተ
ላለማለት ለምን
ግጥሙ ይወቀሳል
ለምን ፊደል ይረክሳል
ሁሉም ስንኝ ቤት አይመታም
ልክ እንደዚህ ግጥም
✧・゚・゚:* ──── * ✧・゚:*
አያምርም ለማለት
መስፈርቱ ይህ ከሆነ
ቆርጣች ቀጥሏት
ቀዳችሁ ስፏት
✾ ❀ ስለሆነችው ሳይሆን
እንድትሆን ወደምትፈልጉት
ምዕናባችሁ ምሯት ❀
✦•≪──── ⋆⋅🌙⋅⋆ ────≫•✦
@getem
@getem
@paappii
>>Click here to continue<<