እንደ እኔ 'ላለ ሰው
እንደ እኔ 'ላለ ሰው
ሃጢያት ለወረሰው
በህንፃ እግዚአብሔር፤በልቡ መንበር ላይ ክፋት ላነገሰው
በአለም ለጠፋ መንገድ ላልመለሰው
ባልጠበቀው ሰዓት መቅሰፍትህ ቢመጣ
ቅጣት ቢያሸብረው መድረሻ ቢያጣ
አምላኩን ቢያስታውስ ፤ከልቡ ቢመለስ
ብሎ ቢጠይቀው "አምላክ ተለመነን መከራውን አስታግስ"
በደሉን ቢረሳ ቢል "እርሱ ይጠብቀኛል"
አሳቡን ቢጥል፤ፍርሃቱን ቢያስወግድ ሸክሙን ቢያቃልል
እንደ እኔ ያለ ሰው
ቀና ብሎ ቢማፀን እርሱን ቢጠይቀው
መልስ ይኖረው ይሆን አምላክ የሚሰጠው?
.
.
.
ለምንወዳቸው ስንል እንጠንቀቅ🙏
21/7/2012 ሶፈ
.
.
.
@getem
@getem
@getem
>>Click here to continue<<