መድሀኒት
""""""""""""
ተስፋን እንድሰንቅ
እፎይ ብዬ እንዳድር ልቤ እንደተመኘ፤
እሰይ አሹ ልበል
አይኔም እንቅልፍ ያግኝ
እስቲ በሉኝና መድሀኒት ተገኘ!
.
"ተገኘ እኮ" በሉኝ
ለሰውም፣ ለምድሩም ፣ለሀገሩም መድሀኒት፤
ለመንደር ፣ለቀዬው፣ ለአድባሩም መድሀኒት፤
ለወፍ፣ ለአራዊቱ ፣ለእንስሳው መድሀኒት፤
ለህፃን ፣ወጣቱ ፣ ለአዋቂው መድሀኒት፤
ኑሮ ኑሮ እንዲሆን
ህይወት እንድትጥም ተስፋን እንድሰነቅ!
.
ህይወት ምን ባትጥም
ካለመሰናክል ስንክሳር ካልኖራት፤
እጥፍ ትጥማለች
ዘዴ ሲገኝላት በሰዎች ብልሀት፤
ለደዌውም ፈውስ ለህመሙም መድሀኒት!
(እናማ)
ተስፋን እንድሰንቅ
እፎይ ብዬ እንዳድር ልቤ እንደተመኘ፤
እሰይ አሹ ልበል
አይኔም እንቅልፍ ያግኝ
እስቲ በሉኝና መድሀኒት ተገኘ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@getem
@getem
@getem
>>Click here to continue<<